
ሐረር፤ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፦በዘመናዊ ቴክኖሎጂና ብቁ የሰው ሃይል በተደራጀ መልኩ ፈጣንና አስተማማኝ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ።
የአየር ትራንስፖርት ደህንነትን አስተማማኝ በማድረግ፤ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራር ከመዘርጋት አንፃር ኢዜአ በድሬደዋ የምስራቅ ማዕከላዊ ሲቪል አቪየሽን የስራ እንቅስቃሴን ቃኝቷል።
በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ እንዳለ አሰፋ፤ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ይበልጥ እያደገ እና እየዘመነ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም ከጊዜው ጋር የሚራመድ ቴክኖሎጂ እና ብቁ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን አንስተው፥ በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል ብለዋል።
በአየር ትራፊክ ማኔጅመንት፣በአቪዬሽን ቁጥጥር እና በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ዘመናዊ አሰራሮችና ቀልጣፋ አገልግሎቶች መኖራቸውን አንስተዋል።
በተለይም በሙያ ክህሎት ስልጠና በኩል ከሀገር ውስጥ አልፎ ለሌሎች የአፍሪካ አገራትም ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፥ በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው የመሪነት ሚናውን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።
የድሬደዋ ምስራቅ ማዕከላዊ ሲቪል አቪዬሽን ተጠባባቂ ሃላፊ አቶ ቴዎድሮስ ክበበው፥የአየር በረራ ደህንነት በየትኛውም ጊዜና ሰዓት በአስተማማኝ መልኩ እየተጠበቀ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህም አስተማማኝ ቴክኖሎጂና በብቃት የሰለጠነ የሰው ሃይል መኖሩን ጠቅሰው፥ በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
የድሬደዋ ምስራቅ ማዕከላዊ ሲቪል አቪዬሽን የበረራ ቅኝት ምህንድስና ቴክኒሻን ሄኖክ ሚካኤል በበኩላቸው፥ የአየር በረራ ደህንነቱ በተጠበቀና በተሳለጠ መልኩ የክትትልና ቁጥጥር ስራው በአስተማማኝ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የአየር በረራ ደህንነት የተሳለጠ እንዲሆን በኮሙኒኬሽን ግንኙነት ዘርፍ 24 ሰዓት እየተሰራ እንደሚገኝ የገለጸችው ደግሞ መሰረት ታከለ ናት።
የዘርፉ ባለሙያ የሆኑት መሰረት ታከለ እና የአፕሮች የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ የሆነው ጌቱ ኑርም፤ ለበረራ ደህንነት በልዩ ትኩረትና ጥንቃቄ በማገልገል ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025