የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በዘመናዊ ቴክኖሎጂና ብቁ የሰው ሃይል በመታገዝ ፈጣንና አስተማማኝ የበረራ አገልግሎት እየተሰጠ ነው

May 30, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፦በዘመናዊ ቴክኖሎጂና ብቁ የሰው ሃይል በተደራጀ መልኩ ፈጣንና አስተማማኝ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ።


የአየር ትራንስፖርት ደህንነትን አስተማማኝ በማድረግ፤ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራር ከመዘርጋት አንፃር ኢዜአ በድሬደዋ የምስራቅ ማዕከላዊ ሲቪል አቪየሽን የስራ እንቅስቃሴን ቃኝቷል።


በኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ እንዳለ አሰፋ፤ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ይበልጥ እያደገ እና እየዘመነ መሆኑን ገልጸዋል።


በመሆኑም ከጊዜው ጋር የሚራመድ ቴክኖሎጂ እና ብቁ የሰው ሃይል አስፈላጊ መሆኑን አንስተው፥ በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን በጥሩ ቁመና ላይ ይገኛል ብለዋል።


በአየር ትራፊክ ማኔጅመንት፣በአቪዬሽን ቁጥጥር እና በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ዘመናዊ አሰራሮችና ቀልጣፋ አገልግሎቶች መኖራቸውን አንስተዋል።


በተለይም በሙያ ክህሎት ስልጠና በኩል ከሀገር ውስጥ አልፎ ለሌሎች የአፍሪካ አገራትም ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው፥ በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው የመሪነት ሚናውን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።


የድሬደዋ ምስራቅ ማዕከላዊ ሲቪል አቪዬሽን ተጠባባቂ ሃላፊ አቶ ቴዎድሮስ ክበበው፥የአየር በረራ ደህንነት በየትኛውም ጊዜና ሰዓት በአስተማማኝ መልኩ እየተጠበቀ መሆኑን ገልጸዋል።


ለዚህም አስተማማኝ ቴክኖሎጂና በብቃት የሰለጠነ የሰው ሃይል መኖሩን ጠቅሰው፥ በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።


የድሬደዋ ምስራቅ ማዕከላዊ ሲቪል አቪዬሽን የበረራ ቅኝት ምህንድስና ቴክኒሻን ሄኖክ ሚካኤል በበኩላቸው፥ የአየር በረራ ደህንነቱ በተጠበቀና በተሳለጠ መልኩ የክትትልና ቁጥጥር ስራው በአስተማማኝ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።


የአየር በረራ ደህንነት የተሳለጠ እንዲሆን በኮሙኒኬሽን ግንኙነት ዘርፍ 24 ሰዓት እየተሰራ እንደሚገኝ የገለጸችው ደግሞ መሰረት ታከለ ናት።


የዘርፉ ባለሙያ የሆኑት መሰረት ታከለ እና የአፕሮች የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ የሆነው ጌቱ ኑርም፤ ለበረራ ደህንነት በልዩ ትኩረትና ጥንቃቄ በማገልገል ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026