የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በዞኑ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች የቡና ልማት ምርታማነትን በእጥፍ አሳድገዋል

Jun 3, 2025

IDOPRESS

ዲላ፤ግንቦት 24/2017 (ኢዜአ)፦በምዕራብ ጉጂ ዞን የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች የቡና ልማት ምርታማነትን በእጥፍ ማሳደጋቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አመለከተ።


በዞኑ የሚገኘው ቀርጫንሼ ግሩፕ ዘመናዊ የቡና እርሻ ከሶስት ሚሊዮን በላይ የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን ለአርሶ አደሮች ማሰራጨት ጀምሯል።


የቡና ስርጭቱም በዞኑ አምስት ወረዳዎች ከሶስት ሺህ የሚልቁ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑም ተመላክቷል።


የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ቱኬ አና በወቅቱ ለኢዜአ እንዳሉት፥በዞኑ የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ ለተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች ልማት ትኩረት ተሰጥቷል።


በተለይም ባለፉት ዓመታት ያረጀና በበሽታ የተጠቃ ቡናን በማንሳት በተሻሻሉ ዝርያዎች ለመተካት በተደረገ ጥረት ሰባት ኩንታል በሄክታር የነበረውን የዞኑን አማካይ ምርታማነት ከእጥፍ በላይ በማሳደግ 15 ኩንታል ማድረስ መቻሉን አስረድተዋል።


በዚህም በዞኑ የቡና ልማት ሽፋኑን ከ141 ሺህ ሄክታር በላይ ማድረስ መቻሉን ጠቁመዋል።


ዞኑ በተያዘው በጀት ዓመት ባለፉት አስር ወራት ከ101 ሺህ ቶን በላይ ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ መቻሉንም ገልጸዋል።


ቀርጫንሼ ግሩፕ ዘመናዊ የቡና እርሻ ዘመናዊ አሰራርን ለዞኑ አርሶ አደሮች ከማስተዋወቅ ባለፈ የተሻሻሉ ዝርያዎችን በማሰራጨት ምርታማነትን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ እንደሚገኝም ሃላፊው ተናግረዋል።


ቀርጫንሼ ግሩፕ ዘመናዊ የቡና እርሻ በጠብታ መስኖ ከሁለት ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና በመሸፈን በሄክታር ከ40 ኩንታል በላይ ምርት እያገኘ መሆኑን ያነሱት ደግሞ በድርጅቱ የሰርተፊኬሽንና ዘላቂ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብዱ ኢታና ናቸው።


ምርቱን በጥራት አዘጋጅቶ ለውጭ ገበያ በማቅረብም ከራሱ አልፎ ሀገርን እየደገፈ መሆኑን አንስተው፥ ተሞክሮውን ለማስፋት በስሩ ከ20 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በማቀፍ የተቀናጀ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ነው ያነሱት።


ዛሬ የመጀመሪያ ምዕራፍ ተጠቃሚ ለሆኑ ከሶስት ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ከሶስት ሚሊዮን የሚልቁ የተሻሻሉ የቡና ችግኞች ስርጭት መደረጉን ጠቅሰው፥ መሰል ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።


በዞኑ የቡሌ ሆራ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ተሰማ ሮባ በበኩላቸው፥ ባለፉት ሶስት ዓመታት ከአራት ሄክታር በላይ ማሳቸውን በተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች መቀየራቸውን ተከትሎ ምርታማነታቸውን በእጥፍ ማሳደጋቸውን አንስተዋል።


በተያዘው ዓመትም ከ1 ሺህ 500 በላይ የተሻሻሉ ዝርያዎችን ለመትከል የጉድጓድ ቁፋሮና የተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን ተናግረዋል።


ከቀርጫንሼ ግሩፕ ያገኙትን የችግኝና የክህሎት ድጋፍ ከልምዳቸው ጋር በማቀናጀት ችግኞችን በመትከልና በመንከባከብ ምርታማነትን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።


ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አርሶ አደር አብዱልቃድር ጉያ በበኩላቸው፥ ቡናን በባህላዊ መንገድ ማልማት ምርታማነት ላይ ጫና እያሳደረ ነው ብለዋል።


በአሁኑ ወቅት ከቀርጫንሼ ግሩፕ ዘመናዊ የእርሻ ልማት ተሞክሮ በመውሰድ የተሻሻሉ ዝርያዎችን በዘመናዊ መንገድ እያለሙ መሆናቸውን አንስተዋል።


ዛሬ ከ400 በላይ የተሻሻሉ ዝርያዎችን መረከባቸውን ጠቅሰው፥ በቀጣይ የተሻለ ምርት ለማግኘት ጥረት እንደሚያደርጉም ተናግረዋል።


የቀርጫንሼ ግሩፕ ዘመናዊ የቡና እርሻ ልማት ከጥላ ዛፍ ውጪ በቴክኖሎጂ በተደገፈ ቡናን በጠብታ መስኖ የማልማት አዲስ አሰራረን ያስተዋወቀ ድርጅት ሲሆን ከዚህ ቀደምም በጠቅላይ ሚኒስትሩና በሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ምልከታ እንደተከናወነለት ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025