
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 24/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሻርጃ ከተማ ዛሬ ማምሻውን የመንገደኞች የበረራ አገልግሎት ጀምሯል።
በሣምንት አራት ጊዜ የሚደረገው ይህ የበረራ አገልግሎት፤ መንገደኞች ወደ ሻርጃ ከተማ በተቀላጠፈ አማራጭ በቀላሉ እንዲጓዙ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመካከለኛው ምሥራቅ ከ17 በላይ መዳረሻዎች እንዳሉት እና ከ100 በላይ ሳምንታዊ የመንገደኞችና የካርጎ አገልግሎት በረራዎችን እያደረገ መሆኑን አስታውቋል፡፡
ወደ ሻርጃ ከተማ የተጀመረው የበረራ አገልግሎት በኢትዮጵያና በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች መካከል ያለውን የንግድ፣ ቱሪዝምና የባህል ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚያስችልም ተጠቅሷል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025