ሚዛን አማን፤ግንቦት 27/2017 (ኢዜአ)፦በሚዛን አማን ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ እንዲፋጠን ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ የከተማው ነዋሪዎች ገለጹ።
ከነዋሪዎቹ መካከል መቶ አለቃ ተስፋዬ ናትናኤል፥ የከተማዋን ገጽታ እየቀየረ ያለውን የኮሪደር ልማት የእግረኛን መንገድ በማስፋትና የመናፈሻ አገልግሎትን ማስፋት ያሰቻለ ሰው ተኮር ፕሮጀክት ነው ብለዋል።
ልማቱ በተሳካ ሁኔታ እንዲፋጠን ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ አስታውቃዋል።
እስከ አሁን የተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ስራዎች የትራንስፖርት እንቅስቃሴን በማቀላጠፍ የተሽከርካሪ አደጋን መቀነስ እንደሚያስችል አስተያየቱን የሰጠው ደግሞ ሌላው የከተማው ነዋሪ ወጣት ታከለ ገብረማሪያም ነው።
ከተማዋን ንጹህ፣አረንጓዴና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ የተጀመረው የኮሪደር ልማት በተሳለጠ ሁኔታ እንዲፋጠን የበኩሉን ድጋፍ እንደሚያጠናክር ተናግሯል።
ወጣት ኤርሚያስ አበበ በበኩሉ፥የከተማዋ የኮሪደር ልማት ሥራን በፍጥነት ለማጠናቀቅ በሚደረገው ርብርብ ድጋፉን እንደሚቀጥል ገልጿል።
የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰሎሞን ሌዊ ፤ በከተማዋ ከተጀመረው የአንድ ኪሎሜትር የኮሪደር ልማት ስራ የጎርፍ መፋሰሻ፣ የአረንጓዴ ልማት እና የእግረኛ መንገድ ስራው በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል ብለዋል።
በኮሪደር ልማት ሥራ ኅብረተሰቡ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቅሰው፥የተጀመሩትን በቅርብ ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ቀጣዩን የኮሪደር ልማት ምዕራፍ ለማስጀመር ከከተማው ኅብረተሰብ ጋር በመቀናጀት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025