የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ለሚተገበሩ አሰራሮች የምናደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል - የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት

Jun 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ለምትተገብራቸው አሰራሮች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) ገለጸ።

በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የምግብና እርሻ ድርጅት የቴክኒክ አማካሪ ጀምስ ስዊራኒ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ለመቻል በምታደርገው ጥረት የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ተግባራዊ ያደረገቻቸው አሰራሮች ተጨባጭ ውጤት አምጥተዋል።


በስንዴ ምርታማነት፣ ግብርናውን ለማዘመን ተግባራዊ የተደረጉ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች እንዲሁም በዘርፉ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች ዘላቂ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) በኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚተገበሩ መርሃ ግብሮችን ለመደገፍ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ምርትን ቀጣይነት ባለው መልኩ በማምረት ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚከናወኑ ተግባራትን እንደሚደግፍም ነው ጀምስ ስዊራኒ የገለጹት።


ድርጅቱ የግብርናና የእንስሳት ጤናና ምርታማነትን ለማሳደግ ተግባራዊ ለሚደረጉ አሰራሮች የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።

ድርጅቱ ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ለመቻል ተግባራዊ ያደረገቻቸውን የሌማት ትሩፋት፣ አረንጓዴ አሻራና ሌሎች መርሃ ግብሮችን በስፋት እንደሚደግፍ አረጋግጠዋል።

የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ላስመዘገበችው ውጤት እውቅና መስጠቱን አስታውሰው በቀጣይም የበለጠ ውጤት እንደምታስመዘግብ እምነታቸው መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025