
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ለምትተገብራቸው አሰራሮች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) ገለጸ።
በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የምግብና እርሻ ድርጅት የቴክኒክ አማካሪ ጀምስ ስዊራኒ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ለመቻል በምታደርገው ጥረት የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ተግባራዊ ያደረገቻቸው አሰራሮች ተጨባጭ ውጤት አምጥተዋል።

በስንዴ ምርታማነት፣ ግብርናውን ለማዘመን ተግባራዊ የተደረጉ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች እንዲሁም በዘርፉ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች ዘላቂ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) በኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚተገበሩ መርሃ ግብሮችን ለመደገፍ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ምርትን ቀጣይነት ባለው መልኩ በማምረት ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚከናወኑ ተግባራትን እንደሚደግፍም ነው ጀምስ ስዊራኒ የገለጹት።

ድርጅቱ የግብርናና የእንስሳት ጤናና ምርታማነትን ለማሳደግ ተግባራዊ ለሚደረጉ አሰራሮች የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።
ድርጅቱ ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ለመቻል ተግባራዊ ያደረገቻቸውን የሌማት ትሩፋት፣ አረንጓዴ አሻራና ሌሎች መርሃ ግብሮችን በስፋት እንደሚደግፍ አረጋግጠዋል።
የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ላስመዘገበችው ውጤት እውቅና መስጠቱን አስታውሰው በቀጣይም የበለጠ ውጤት እንደምታስመዘግብ እምነታቸው መሆኑን ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025