የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ለሚተገበሩ አሰራሮች የምናደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል - የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት

Jun 5, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ለምትተገብራቸው አሰራሮች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) ገለጸ።

በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የምግብና እርሻ ድርጅት የቴክኒክ አማካሪ ጀምስ ስዊራኒ ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ለመቻል በምታደርገው ጥረት የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ ተግባራዊ ያደረገቻቸው አሰራሮች ተጨባጭ ውጤት አምጥተዋል።


በስንዴ ምርታማነት፣ ግብርናውን ለማዘመን ተግባራዊ የተደረጉ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች እንዲሁም በዘርፉ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች ዘላቂ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ መሰረት የሚጥሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) በኢትዮጵያ የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚተገበሩ መርሃ ግብሮችን ለመደገፍ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ምርትን ቀጣይነት ባለው መልኩ በማምረት ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚከናወኑ ተግባራትን እንደሚደግፍም ነው ጀምስ ስዊራኒ የገለጹት።


ድርጅቱ የግብርናና የእንስሳት ጤናና ምርታማነትን ለማሳደግ ተግባራዊ ለሚደረጉ አሰራሮች የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል ብለዋል።

ድርጅቱ ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ለመቻል ተግባራዊ ያደረገቻቸውን የሌማት ትሩፋት፣ አረንጓዴ አሻራና ሌሎች መርሃ ግብሮችን በስፋት እንደሚደግፍ አረጋግጠዋል።

የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ላስመዘገበችው ውጤት እውቅና መስጠቱን አስታውሰው በቀጣይም የበለጠ ውጤት እንደምታስመዘግብ እምነታቸው መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025