የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

አመራሩ በክልሉ የተመዘገቡ ውጤቶችን በብቃት መምራትና ማስቀጠል ይኖርበታል

Jun 6, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ግንቦት 28/2017 (ኢዜአ)፦አመራሩ በክልሉ የተመዘገቡ ውጤቶችን በብቃትና በቁርጠኝነት መምራትና አጠናክሮ ለማስቀጠል መረባረብ እንደሚገባው ተገልጿል።


“ብቁ አመራር መገንባት ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ በሲዳማ ክልል ለሚገኙ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በሀዋሳ ስልጠና እየተሰጠ ነው።


በዚህም በሲዳማ ክልል የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ብቃት ባለው አመራር የተመዘገቡ ውጤቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል መረባረብ እንደሚገባ ተመላክቷል።


በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ በወቅቱ እንዳሉት፥ በክልሉ የቤተሰብ ብልጽግናን ለማምጣት የተጀመረው ስራ ስኬታማ እንዲሆን አመራሩ በብቃትና በቁርጠኝነት መምራት እንዳለበትም ተናግረዋል።


በአገር አቀፍም ሆነ በክልል ደረጃ አመራሩ ማህበረሰቡን በማስተባበር የተመዘገቡ ውጤቶችና የመጡ ለውጦች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መትጋት ይገባዋል ብለዋል።


በክልል ደረጃ የቤተሰብ ብልጽግናን ለማምጣት 68 ፓኬጆች ያሉት 8 ኢንሺዬቲቮች ተቀርጸው ወደ ተግባር መገባቱን የገለፁት ኃላፊው ከኢንሼቲቮቹ አንዱ በሆነው በሌማት ትሩፋት በተለይም በዶሮና የወተት ላም እርባታ፣ በንብ ማነብና በዓሳ እርባታ ረገድ ውጤታማ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።


ለሁለት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ላይ ከክልል እስከ ዞን ያሉ ከፍተኛ አመራር አባላት እየተሳተፉ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025