ሀዋሳ፤ግንቦት 28/2017 (ኢዜአ)፦አመራሩ በክልሉ የተመዘገቡ ውጤቶችን በብቃትና በቁርጠኝነት መምራትና አጠናክሮ ለማስቀጠል መረባረብ እንደሚገባው ተገልጿል።
“ብቁ አመራር መገንባት ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ በሲዳማ ክልል ለሚገኙ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በሀዋሳ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
በዚህም በሲዳማ ክልል የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ብቃት ባለው አመራር የተመዘገቡ ውጤቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል መረባረብ እንደሚገባ ተመላክቷል።
በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ በወቅቱ እንዳሉት፥ በክልሉ የቤተሰብ ብልጽግናን ለማምጣት የተጀመረው ስራ ስኬታማ እንዲሆን አመራሩ በብቃትና በቁርጠኝነት መምራት እንዳለበትም ተናግረዋል።
በአገር አቀፍም ሆነ በክልል ደረጃ አመራሩ ማህበረሰቡን በማስተባበር የተመዘገቡ ውጤቶችና የመጡ ለውጦች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መትጋት ይገባዋል ብለዋል።
በክልል ደረጃ የቤተሰብ ብልጽግናን ለማምጣት 68 ፓኬጆች ያሉት 8 ኢንሺዬቲቮች ተቀርጸው ወደ ተግባር መገባቱን የገለፁት ኃላፊው ከኢንሼቲቮቹ አንዱ በሆነው በሌማት ትሩፋት በተለይም በዶሮና የወተት ላም እርባታ፣ በንብ ማነብና በዓሳ እርባታ ረገድ ውጤታማ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።
ለሁለት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ላይ ከክልል እስከ ዞን ያሉ ከፍተኛ አመራር አባላት እየተሳተፉ ይገኛል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025