
ሀዋሳ፤ግንቦት 28/2017 (ኢዜአ)፦አመራሩ በክልሉ የተመዘገቡ ውጤቶችን በብቃትና በቁርጠኝነት መምራትና አጠናክሮ ለማስቀጠል መረባረብ እንደሚገባው ተገልጿል።
“ብቁ አመራር መገንባት ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ በሲዳማ ክልል ለሚገኙ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በሀዋሳ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
በዚህም በሲዳማ ክልል የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ብቃት ባለው አመራር የተመዘገቡ ውጤቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል መረባረብ እንደሚገባ ተመላክቷል።
በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ በወቅቱ እንዳሉት፥ በክልሉ የቤተሰብ ብልጽግናን ለማምጣት የተጀመረው ስራ ስኬታማ እንዲሆን አመራሩ በብቃትና በቁርጠኝነት መምራት እንዳለበትም ተናግረዋል።
በአገር አቀፍም ሆነ በክልል ደረጃ አመራሩ ማህበረሰቡን በማስተባበር የተመዘገቡ ውጤቶችና የመጡ ለውጦች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መትጋት ይገባዋል ብለዋል።
በክልል ደረጃ የቤተሰብ ብልጽግናን ለማምጣት 68 ፓኬጆች ያሉት 8 ኢንሺዬቲቮች ተቀርጸው ወደ ተግባር መገባቱን የገለፁት ኃላፊው ከኢንሼቲቮቹ አንዱ በሆነው በሌማት ትሩፋት በተለይም በዶሮና የወተት ላም እርባታ፣ በንብ ማነብና በዓሳ እርባታ ረገድ ውጤታማ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።
ለሁለት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ላይ ከክልል እስከ ዞን ያሉ ከፍተኛ አመራር አባላት እየተሳተፉ ይገኛል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025