
ሀዋሳ፤ግንቦት 28/2017 (ኢዜአ)፦አመራሩ በክልሉ የተመዘገቡ ውጤቶችን በብቃትና በቁርጠኝነት መምራትና አጠናክሮ ለማስቀጠል መረባረብ እንደሚገባው ተገልጿል።
“ብቁ አመራር መገንባት ለሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ሃሳብ በሲዳማ ክልል ለሚገኙ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በሀዋሳ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
በዚህም በሲዳማ ክልል የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ብቃት ባለው አመራር የተመዘገቡ ውጤቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል መረባረብ እንደሚገባ ተመላክቷል።
በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ በወቅቱ እንዳሉት፥ በክልሉ የቤተሰብ ብልጽግናን ለማምጣት የተጀመረው ስራ ስኬታማ እንዲሆን አመራሩ በብቃትና በቁርጠኝነት መምራት እንዳለበትም ተናግረዋል።
በአገር አቀፍም ሆነ በክልል ደረጃ አመራሩ ማህበረሰቡን በማስተባበር የተመዘገቡ ውጤቶችና የመጡ ለውጦች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መትጋት ይገባዋል ብለዋል።
በክልል ደረጃ የቤተሰብ ብልጽግናን ለማምጣት 68 ፓኬጆች ያሉት 8 ኢንሺዬቲቮች ተቀርጸው ወደ ተግባር መገባቱን የገለፁት ኃላፊው ከኢንሼቲቮቹ አንዱ በሆነው በሌማት ትሩፋት በተለይም በዶሮና የወተት ላም እርባታ፣ በንብ ማነብና በዓሳ እርባታ ረገድ ውጤታማ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል።
ለሁለት ቀናት በሚቆየው ስልጠና ላይ ከክልል እስከ ዞን ያሉ ከፍተኛ አመራር አባላት እየተሳተፉ ይገኛል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026