የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በመዲናዋ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ ልማቶች የከተማዋን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትና የቱሪስት ፍሰትን የሚጨምር ነው - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች

Jun 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ ልማቶች የከተማዋን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትና የቱሪስትን ፍሰትን የሚጨምሩ መሆናቸውን ኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች ገለጹ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ትረስት ፈንድ ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር በከተማው የተሰሩና እየተሰሩ ያሉትን ሰው ቶኮር ልማቶች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡


በአየር መንገዱ የሰራተኞች ተግባቦትና የውስጥ ኮሙኒኬሽን ማናጀር አቶ ሰለሞን ገብረመድን በጉብኝቱ ወቅት፤ አየር መንገዱ በየዓመቱ የሰራተኞችን ቀን እንደሚያከብር አስታውሰው፤ ዘንድሮም ሳምንቱን ሙሉ በተለያዩ ዝግጅቶች ለማክበር ታቅዶ እየተከበረ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡

የዛሬው ጉብኝትም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ሰራተኞቹ በከተማው ውስጥ ያሉ ልማቶችን ተገንዝበው በሄዱበት ዓለም ዳርቻ ሁሉ ሀገራችንን ለማስተዋወቅ የድርሻችንን እንድንወጣ ያለመ ነው ብለዋል ፡፡

በጉብኝቱም ተጠናክሮ ሊቀጥሉ የሚገቡ አስደማሚ ልማቶች መመልከታቸውንም ገልጸዋል ፡፡

አየር መንገዱ ከከተማ አስተዳደሩ የማህበራዊ ትረስት ፈንድ ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር የተለያዩ ሰው ቶከር ልማቶችን እየደገፈ መሆኑንና ይህንም አጠናክሮ እንደሚቀጥሉ ነው የገለጹት፡፡


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ማህበራዊ ትረስት ፈንድ ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ አስራት ንጉሴ በበኩላቸው ፤ የከተማው ነዋሪና ሁሉም ዜጋ በከተማው ልማት ላይ በመሳተፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ የሚያስችል ተግባር እያከናወኑ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡

ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ተጋላጭ የሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎችን በዘላቂነት የማቋቋም ተግባርም እያተከናወነ መሆኑን አክለዋል፡፡

በዛሬው ጉብኝት የአየር መንገዱ ሰራተኞች በከተማው ውስጥ የሚሰሩ ልማቶች ላይ ግንዛቤ የፈጠረና በሰው ተኮር ልማት ላይ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ግንዛቤ የተፈጠረበት ነው ብለዋል ፡፡


በአየር መንገዱ የአቬየሽን ዩኒቨርርሲቲ የፓይለት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ኃላፊ ካፒቴን አብርሃም አከለ ፤ አዲስ አበባን ከዓለም አቀፍ ከተሞች ጋር ተወዳዳሪ የሚያደርጉ ልማቶች መገንዘቡን ተናግሯል፡፡

በከተማው በተሰሩ የኮሪደር ልማቶች፣ ሕብረተሰቡን የሚጠቅሙ መዝናኛዎችና በሰው ተኮር ልማቶች መደመማቸውን የገለጹት በአየር መንገዱ የሰው ሃብት ክፍል ባለሙያ ወይዘሮ ቅድስት ጌታሁን ናቸው ፡፡


በከተማው የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ ልማቶች ከተማዋን ለነዋሪዋቿ ምቹና ፅዱ የሚያደርግና ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ትልቅ ድርሻ ያለው የቱሪስት ፍሰት እንዲጨምር የሚያደርግ ነው ብለዋል ፡፡

በመርሃ ግብሩም አየር መንገድ ሰራተኞች መኖሪያ ህንጻ ግንባታ የደረሰበት ደረጃ፣ የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል፤ የኮሪደር ልማት መንገዶች፣ መዝናኛዎች፣ የመኪና ማቆሚያ ህንጻ፣ ተስፋ የአረጋዊያንና አቅመ ደካሞች ምገባ ማዕከልን ጎብኝተዋል ።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025