የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ከተረጂነት ነጻ የመውጣት ራዕይ እንዲሳካ ኢትዮጵያውያን የላቀ ጥረት ሊያደርጉ ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Jun 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ሙሉ ለሙሉ በማላቀቅ ራሷን እንድትችል የተያዘው ግብ እንዲሳካ ኢትዮጵያውያን በላቀ ትጋት እንዲሰሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ልዩ ቆይታ ተረጂነት የኢትዮጵያ አደገኛ ስብራት ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ራስን ከመለወጥ ይልቅ ሌሎችን በመለመንና በመጠበቅ መኖር ትልቅ የስነ-ልቦና ስብራት መሆኑንም አመልክተዋል።

ኢትዮጵያን የሚያክል ትልቅ ሀገር ራሷን መመገብ እና ራሷን መቻል አቅቷት ሌሎችን መለመኗ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ ነው ብለዋል።

እኛ ተረድተን ተረጂነትን ማውረስ የለብንም እኛ ለምነን ልመናን ማሸጋገር የለብንም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተረጂነት እኛ ጋር መቆም አለበት ሲሉም ገልጸዋል።

መንግስት ተረጂነት የፈጠረውን ከፍተኛ ስብራት በመጠገን ከተረጂነት መውጣት ብቻ ሳይሆን ረጂ በመሆን ለውጥ ማምጣት አለብን የሚል ጽኑ አቋም መያዙንም ተናግረዋል።

ይህንን ከግምት በማስገባትም እስከ ታችኛው የአስተዳደር እርከን በመውረድ በጉዳዩ ላይ ከህዝብ ጋር ሰፊ ውይይት መካሄዱን ጠቅሰው ከህዝቡ የተገኘው ምላሽ የሚያስደስት እንደነበር ነው ያወሱት።

እንፍጠን፣ እንፍጠር እና እንስራ ይብቃን ልመና የኢትዮጵያውያን የወል ድምጽ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተረጂነት መላቀቅ የመንግስት እና የጋራ አቋም መሆኑን አንስተዋል።

መንግስት እና ህዝብ ከተረጂነት ለመላቀቅ ባከናወኑት ስራ የሚታዩ ተጨባጭ ለውጦች መምጣታቸውን ገልጸዋል።

ለዚህም በ2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ 27 ሚሊዮን ገደማ ተረጂ እንደነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ አሃዝ በ2017 ዓ.ም ወደ 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዝቅ ማለቱን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

23 ሚሊዮን ህዝብ ከተረጂነት ማውጣት የኢትዮጵያ ማንሰራራት አንዱ ማሳያ እንደሆነ ጠቅሰው የተገኘው ስኬት ትልቅ ድል መሆኑንም አስረድተዋል።

መንግስት በጥቂት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ሙሉ ለሙሉ የማላቀቅ ግብ አስቀምጦ እየሰራ እንደሆነም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ያነሱት።

ከተረጂነት ተላቆ ራስን በመቻል አልፎም ሌሎችን ለመርዳት የተያዘውን ውጥን ለማሳካት ህዝቡ የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላለፍዋል።

#Ethiopian_News_Agency


#ኢዜአ #Ethiopia

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025