
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ሙሉ ለሙሉ በማላቀቅ ራሷን እንድትችል የተያዘው ግብ እንዲሳካ ኢትዮጵያውያን በላቀ ትጋት እንዲሰሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ልዩ ቆይታ ተረጂነት የኢትዮጵያ አደገኛ ስብራት ነው ሲሉ ገልጸዋል።
ራስን ከመለወጥ ይልቅ ሌሎችን በመለመንና በመጠበቅ መኖር ትልቅ የስነ-ልቦና ስብራት መሆኑንም አመልክተዋል።
ኢትዮጵያን የሚያክል ትልቅ ሀገር ራሷን መመገብ እና ራሷን መቻል አቅቷት ሌሎችን መለመኗ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ ነው ብለዋል።
እኛ ተረድተን ተረጂነትን ማውረስ የለብንም እኛ ለምነን ልመናን ማሸጋገር የለብንም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተረጂነት እኛ ጋር መቆም አለበት ሲሉም ገልጸዋል።
መንግስት ተረጂነት የፈጠረውን ከፍተኛ ስብራት በመጠገን ከተረጂነት መውጣት ብቻ ሳይሆን ረጂ በመሆን ለውጥ ማምጣት አለብን የሚል ጽኑ አቋም መያዙንም ተናግረዋል።
ይህንን ከግምት በማስገባትም እስከ ታችኛው የአስተዳደር እርከን በመውረድ በጉዳዩ ላይ ከህዝብ ጋር ሰፊ ውይይት መካሄዱን ጠቅሰው ከህዝቡ የተገኘው ምላሽ የሚያስደስት እንደነበር ነው ያወሱት።
እንፍጠን፣ እንፍጠር እና እንስራ ይብቃን ልመና የኢትዮጵያውያን የወል ድምጽ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተረጂነት መላቀቅ የመንግስት እና የጋራ አቋም መሆኑን አንስተዋል።
መንግስት እና ህዝብ ከተረጂነት ለመላቀቅ ባከናወኑት ስራ የሚታዩ ተጨባጭ ለውጦች መምጣታቸውን ገልጸዋል።
ለዚህም በ2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ 27 ሚሊዮን ገደማ ተረጂ እንደነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ አሃዝ በ2017 ዓ.ም ወደ 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዝቅ ማለቱን በማሳያነት ጠቅሰዋል።
23 ሚሊዮን ህዝብ ከተረጂነት ማውጣት የኢትዮጵያ ማንሰራራት አንዱ ማሳያ እንደሆነ ጠቅሰው የተገኘው ስኬት ትልቅ ድል መሆኑንም አስረድተዋል።
መንግስት በጥቂት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ሙሉ ለሙሉ የማላቀቅ ግብ አስቀምጦ እየሰራ እንደሆነም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ያነሱት።
ከተረጂነት ተላቆ ራስን በመቻል አልፎም ሌሎችን ለመርዳት የተያዘውን ውጥን ለማሳካት ህዝቡ የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላለፍዋል።
#Ethiopian_News_Agency
#ኢዜአ #Ethiopia
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026