የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ከተረጂነት ነጻ የመውጣት ራዕይ እንዲሳካ ኢትዮጵያውያን የላቀ ጥረት ሊያደርጉ ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Jun 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ሙሉ ለሙሉ በማላቀቅ ራሷን እንድትችል የተያዘው ግብ እንዲሳካ ኢትዮጵያውያን በላቀ ትጋት እንዲሰሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አስገነዘቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ልዩ ቆይታ ተረጂነት የኢትዮጵያ አደገኛ ስብራት ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ራስን ከመለወጥ ይልቅ ሌሎችን በመለመንና በመጠበቅ መኖር ትልቅ የስነ-ልቦና ስብራት መሆኑንም አመልክተዋል።

ኢትዮጵያን የሚያክል ትልቅ ሀገር ራሷን መመገብ እና ራሷን መቻል አቅቷት ሌሎችን መለመኗ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ ነው ብለዋል።

እኛ ተረድተን ተረጂነትን ማውረስ የለብንም እኛ ለምነን ልመናን ማሸጋገር የለብንም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተረጂነት እኛ ጋር መቆም አለበት ሲሉም ገልጸዋል።

መንግስት ተረጂነት የፈጠረውን ከፍተኛ ስብራት በመጠገን ከተረጂነት መውጣት ብቻ ሳይሆን ረጂ በመሆን ለውጥ ማምጣት አለብን የሚል ጽኑ አቋም መያዙንም ተናግረዋል።

ይህንን ከግምት በማስገባትም እስከ ታችኛው የአስተዳደር እርከን በመውረድ በጉዳዩ ላይ ከህዝብ ጋር ሰፊ ውይይት መካሄዱን ጠቅሰው ከህዝቡ የተገኘው ምላሽ የሚያስደስት እንደነበር ነው ያወሱት።

እንፍጠን፣ እንፍጠር እና እንስራ ይብቃን ልመና የኢትዮጵያውያን የወል ድምጽ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተረጂነት መላቀቅ የመንግስት እና የጋራ አቋም መሆኑን አንስተዋል።

መንግስት እና ህዝብ ከተረጂነት ለመላቀቅ ባከናወኑት ስራ የሚታዩ ተጨባጭ ለውጦች መምጣታቸውን ገልጸዋል።

ለዚህም በ2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ 27 ሚሊዮን ገደማ ተረጂ እንደነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህ አሃዝ በ2017 ዓ.ም ወደ 3 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዝቅ ማለቱን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

23 ሚሊዮን ህዝብ ከተረጂነት ማውጣት የኢትዮጵያ ማንሰራራት አንዱ ማሳያ እንደሆነ ጠቅሰው የተገኘው ስኬት ትልቅ ድል መሆኑንም አስረድተዋል።

መንግስት በጥቂት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ከተረጂነት ሙሉ ለሙሉ የማላቀቅ ግብ አስቀምጦ እየሰራ እንደሆነም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው ያነሱት።

ከተረጂነት ተላቆ ራስን በመቻል አልፎም ሌሎችን ለመርዳት የተያዘውን ውጥን ለማሳካት ህዝቡ የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት አስተላለፍዋል።

#Ethiopian_News_Agency


#ኢዜአ #Ethiopia

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026