
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2017 (ኢዜአ)፦ አዲስ አበባፅዱ፣ ውብ እና ለመኖር ምቹ ለጎብኚዎችም ተመራጭ እስከምትሆን ሌት ተቀን መትጋታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከከንቲባ አዳነች አቤቤ ጋር በመሆን ከአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ እና የጎሮ አደባባይ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በመጎብኘት ለህዝብ አገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
ከአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ እና የጎሮ አደባባይ የኮሪደር ልማት ለሕዝብ በገባነው ቃል መሰረት እና ሕዝብን ባሳተፈ መንገድ በተያዘለት ጊዜ መከናወኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።

አዲስ አበባፅዱ፣ ውብ እና ለመኖር ምቹ ለጎብኚዎችም ተመራጭ እስከምትሆን ሌት ተቀን መትጋታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል ከንቲባ አዳነች በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት።
የአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ እና የጎሮ አደባባይ የኮሪደር ልማት ከስምንት ኮሪደሮች አንዱ መሆኑንም አመልክተዋል።
በኮሪደር ልማቱ የ4 ኪሎ ሜትር የሳይክል መንገድ፤ ከ8 ኪሎ ሜትር በላይ ደረጃውን የጠበቀ የእግረኛ መንገድ፤ 3 የመኪና ማቆሚያ ፓርኪንግ ስፍራዎች፣ የህፃናት መጫወቻዎች፣ 7 ፕላዛዎች፣ 6 የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች፣ ፋውንቴኖች 13 ታክሲ መጫኛና ማውረጃ ቦታዎች፣ 872 ሱቆች እና የህዝብ ማረፊያ ክፍት ቦታዎች እና የንግድ ቤቶች ያካተተ መሆኑንመ ገልጸዋል።
መስመሩ የትራፊክ ፍሰት መጨናነቅ የሚታይበት ለአደጋ የተጋለጠና አስቸጋሪ እንደነበር ያወሱት ከንቲባዋ አሁን ላይ የትራፊክ ፍሰቱን የተሳለጠ በሚያደርግ ሁኔታ ስራው መከወኑንም ነው የገለጹት።

ከመንገድ ዳር ያላቸው ርቀት እና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚነት ታሳቢ ያደረገ አካታች መሰረተ ልማቶች መገንባታቸውን አብራርተዋል።
ከጎሮ ዋና መስመር ለሚመጡ ተሸከርካሪዎችና ከቦሌ ዓለም አቀፍ በረራ ተርሚናል በኩል የሚመጡ ተሽከርካሪዎችን በማስተንፈስ ለከተማዋ የትራፊክ መጨናነቅ መፍትሔ እንደሚሰጥም ነው ያስረዱት።
በተጨማሪም በርካታ አነስተኛ የንግድ ስራዎች በአካባቢው መኖራቸው በሺዎች ለሚቆጠሩ ነዋሪዎች ቋሚ የስራእድል እንዲፈጠር ማድረጉንም ጠቁመዋል።

ሁሌም ህዝብን መሠረት ያደረገ ልማት መስራታችን ብቻ ሳይሆን ለትውልዱ የምናስረክባት አዲስ አበባ ፅዱ፣ ውብ እና ለመኖር ምቹ እንዲሁም ለጎብኚዎች ተመራጭ እስከምትሆን ሌት ተቀን መትጋታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።
የከተማው ነዋሪ ለልማት ስራው እያደረገ ላለው ድጋፍም ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምስጋና አቅርበዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026