የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አዲስ አበባ ፅዱ፣ ውብ እና ለመኖር ምቹ ለጎብኚዎችም ተመራጭ እስከምትሆን ሌት ተቀን መትጋታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Jun 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2017 (ኢዜአ)፦ አዲስ አበባፅዱ፣ ውብ እና ለመኖር ምቹ ለጎብኚዎችም ተመራጭ እስከምትሆን ሌት ተቀን መትጋታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከከንቲባ አዳነች አቤቤ ጋር በመሆን ከአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ እና የጎሮ አደባባይ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በመጎብኘት ለህዝብ አገልግሎት ክፍት ተደርጓል።

ከአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ እና የጎሮ አደባባይ የኮሪደር ልማት ለሕዝብ በገባነው ቃል መሰረት እና ሕዝብን ባሳተፈ መንገድ በተያዘለት ጊዜ መከናወኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል።


አዲስ አበባፅዱ፣ ውብ እና ለመኖር ምቹ ለጎብኚዎችም ተመራጭ እስከምትሆን ሌት ተቀን መትጋታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል ከንቲባ አዳነች በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት።

የአንበሳ ጋራዥ-ጃክሮስ እና የጎሮ አደባባይ የኮሪደር ልማት ከስምንት ኮሪደሮች አንዱ መሆኑንም አመልክተዋል።

በኮሪደር ልማቱ የ4 ኪሎ ሜትር የሳይክል መንገድ፤ ከ8 ኪሎ ሜትር በላይ ደረጃውን የጠበቀ የእግረኛ መንገድ፤ 3 የመኪና ማቆሚያ ፓርኪንግ ስፍራዎች፣ የህፃናት መጫወቻዎች፣ 7 ፕላዛዎች፣ 6 የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች፣ ፋውንቴኖች 13 ታክሲ መጫኛና ማውረጃ ቦታዎች፣ 872 ሱቆች እና የህዝብ ማረፊያ ክፍት ቦታዎች እና የንግድ ቤቶች ያካተተ መሆኑንመ ገልጸዋል።

መስመሩ የትራፊክ ፍሰት መጨናነቅ የሚታይበት ለአደጋ የተጋለጠና አስቸጋሪ እንደነበር ያወሱት ከንቲባዋ አሁን ላይ የትራፊክ ፍሰቱን የተሳለጠ በሚያደርግ ሁኔታ ስራው መከወኑንም ነው የገለጹት።


ከመንገድ ዳር ያላቸው ርቀት እና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚነት ታሳቢ ያደረገ አካታች መሰረተ ልማቶች መገንባታቸውን አብራርተዋል።

ከጎሮ ዋና መስመር ለሚመጡ ተሸከርካሪዎችና ከቦሌ ዓለም አቀፍ በረራ ተርሚናል በኩል የሚመጡ ተሽከርካሪዎችን በማስተንፈስ ለከተማዋ የትራፊክ መጨናነቅ መፍትሔ እንደሚሰጥም ነው ያስረዱት።

በተጨማሪም በርካታ አነስተኛ የንግድ ስራዎች በአካባቢው መኖራቸው በሺዎች ለሚቆጠሩ ነዋሪዎች ቋሚ የስራእድል እንዲፈጠር ማድረጉንም ጠቁመዋል።


ሁሌም ህዝብን መሠረት ያደረገ ልማት መስራታችን ብቻ ሳይሆን ለትውልዱ የምናስረክባት አዲስ አበባ ፅዱ፣ ውብ እና ለመኖር ምቹ እንዲሁም ለጎብኚዎች ተመራጭ እስከምትሆን ሌት ተቀን መትጋታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

የከተማው ነዋሪ ለልማት ስራው እያደረገ ላለው ድጋፍም ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026