ነገሌ ቦረና፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን የድርቅ ተጋላጭነትን በዘላቂ ልማት ለመቋቋም በ25ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ መከናወኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተፈጥሮ ሀብት ቡድን መሪ ወንዶ ሸርቦቴ፤ ዘንድሮ 267 ተፋሰሶችን መሰረት ያደረገ 25ሺህ 467 ሄክታር መሬትን የሚያካልል የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡
የእርከን ስራ፣ በጎርፍ የተቦረቦሩ መሬቶችን ማልማት፣ የችግኝ ዝግጅት፣ በተደጋጋሚ የተጎዳ የግጦሽ ሳር ልማትና ምንጭ ማጎልበት ዋና ዋና ስራዎች እንደነበሩ ጠቁመዋል፡፡
እስካሁንም 17ሺህ 141 ኪሎ ሜትር የእርከን እንዲሁም በጎርፍ የተሸረሸሩ የመሬት ክፍሎችን የማልማት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም ለበጋ ወራት አገልግሎት የሚሰጡ ምንጮች መጎልበታቸውን፣ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች ዝግጅትም ጎን ለጎን ሲከናወን መቆየቱን ገልጸዋል።
ተፋሰሶቹን በእጽዋት በመሸፈን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ማዘጋጀትም የስራው አካል መሆኑን አመልክተዋል፡፡
በተፋሰስ ልማት ስራው ከ185ሺህ 200 በላይ ወጣቶች፣ ሴቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል፡፡
በተያያዘም በዘንድሮ የበጋ ወራት በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች ከ11ሺህ ሄክታር በላይ የግጦሽ ሳር መሬት ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ተከልሏል ብለዋል፡፡
የተከለለው የግጦሽ ሳር ልማት በበጋ ወራት ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን ከ55ሺህ የሚበልጥ የቤት እንስሳትን ተጠቃሚ የማድረግ አቅም ያለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዞኑ በድርቅ ተጋላጭ ከመሆን እና ከዝናብ እጥረት የሚያጋጥም የመኖ እጥረት በቤት እንስሳት ላይ ጉዳት እንደሚያደርስ አስታውሰዋል፡፡
ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ ችግሩን በዘላቂ ልማት ለመቋቋም በዞኑ ህዝብ ተሳትፎ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ልማት ስራ በመካሄድ ላይ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025