የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በጉጂ ዞን የድርቅ ተጋላጭነትን በዘላቂ ልማት ለመቋቋም በ25ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ ተከናውኗል

Jun 11, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን የድርቅ ተጋላጭነትን በዘላቂ ልማት ለመቋቋም በ25ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ መከናወኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡


በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተፈጥሮ ሀብት ቡድን መሪ ወንዶ ሸርቦቴ፤ ዘንድሮ 267 ተፋሰሶችን መሰረት ያደረገ 25ሺህ 467 ሄክታር መሬትን የሚያካልል የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡


የእርከን ስራ፣ በጎርፍ የተቦረቦሩ መሬቶችን ማልማት፣ የችግኝ ዝግጅት፣ በተደጋጋሚ የተጎዳ የግጦሽ ሳር ልማትና ምንጭ ማጎልበት ዋና ዋና ስራዎች እንደነበሩ ጠቁመዋል፡፡


እስካሁንም 17ሺህ 141 ኪሎ ሜትር የእርከን እንዲሁም በጎርፍ የተሸረሸሩ የመሬት ክፍሎችን የማልማት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡


በተጨማሪም ለበጋ ወራት አገልግሎት የሚሰጡ ምንጮች መጎልበታቸውን፣ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች ዝግጅትም ጎን ለጎን ሲከናወን መቆየቱን ገልጸዋል።


ተፋሰሶቹን በእጽዋት በመሸፈን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ማዘጋጀትም የስራው አካል መሆኑን አመልክተዋል፡፡


በተፋሰስ ልማት ስራው ከ185ሺህ 200 በላይ ወጣቶች፣ ሴቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል፡፡


በተያያዘም በዘንድሮ የበጋ ወራት በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች ከ11ሺህ ሄክታር በላይ የግጦሽ ሳር መሬት ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ተከልሏል ብለዋል፡፡


የተከለለው የግጦሽ ሳር ልማት በበጋ ወራት ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን ከ55ሺህ የሚበልጥ የቤት እንስሳትን ተጠቃሚ የማድረግ አቅም ያለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በዞኑ በድርቅ ተጋላጭ ከመሆን እና ከዝናብ እጥረት የሚያጋጥም የመኖ እጥረት በቤት እንስሳት ላይ ጉዳት እንደሚያደርስ አስታውሰዋል፡፡


ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ ችግሩን በዘላቂ ልማት ለመቋቋም በዞኑ ህዝብ ተሳትፎ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ልማት ስራ በመካሄድ ላይ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026