ነገሌ ቦረና፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን የድርቅ ተጋላጭነትን በዘላቂ ልማት ለመቋቋም በ25ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ መከናወኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተፈጥሮ ሀብት ቡድን መሪ ወንዶ ሸርቦቴ፤ ዘንድሮ 267 ተፋሰሶችን መሰረት ያደረገ 25ሺህ 467 ሄክታር መሬትን የሚያካልል የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡
የእርከን ስራ፣ በጎርፍ የተቦረቦሩ መሬቶችን ማልማት፣ የችግኝ ዝግጅት፣ በተደጋጋሚ የተጎዳ የግጦሽ ሳር ልማትና ምንጭ ማጎልበት ዋና ዋና ስራዎች እንደነበሩ ጠቁመዋል፡፡
እስካሁንም 17ሺህ 141 ኪሎ ሜትር የእርከን እንዲሁም በጎርፍ የተሸረሸሩ የመሬት ክፍሎችን የማልማት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም ለበጋ ወራት አገልግሎት የሚሰጡ ምንጮች መጎልበታቸውን፣ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች ዝግጅትም ጎን ለጎን ሲከናወን መቆየቱን ገልጸዋል።
ተፋሰሶቹን በእጽዋት በመሸፈን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ማዘጋጀትም የስራው አካል መሆኑን አመልክተዋል፡፡
በተፋሰስ ልማት ስራው ከ185ሺህ 200 በላይ ወጣቶች፣ ሴቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል፡፡
በተያያዘም በዘንድሮ የበጋ ወራት በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች ከ11ሺህ ሄክታር በላይ የግጦሽ ሳር መሬት ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ተከልሏል ብለዋል፡፡
የተከለለው የግጦሽ ሳር ልማት በበጋ ወራት ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን ከ55ሺህ የሚበልጥ የቤት እንስሳትን ተጠቃሚ የማድረግ አቅም ያለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዞኑ በድርቅ ተጋላጭ ከመሆን እና ከዝናብ እጥረት የሚያጋጥም የመኖ እጥረት በቤት እንስሳት ላይ ጉዳት እንደሚያደርስ አስታውሰዋል፡፡
ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ ችግሩን በዘላቂ ልማት ለመቋቋም በዞኑ ህዝብ ተሳትፎ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ልማት ስራ በመካሄድ ላይ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025