የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በጉጂ ዞን የድርቅ ተጋላጭነትን በዘላቂ ልማት ለመቋቋም በ25ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ ተከናውኗል

Jun 11, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን የድርቅ ተጋላጭነትን በዘላቂ ልማት ለመቋቋም በ25ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ መከናወኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡


በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የተፈጥሮ ሀብት ቡድን መሪ ወንዶ ሸርቦቴ፤ ዘንድሮ 267 ተፋሰሶችን መሰረት ያደረገ 25ሺህ 467 ሄክታር መሬትን የሚያካልል የአፈርና ውሀ ጥበቃ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡


የእርከን ስራ፣ በጎርፍ የተቦረቦሩ መሬቶችን ማልማት፣ የችግኝ ዝግጅት፣ በተደጋጋሚ የተጎዳ የግጦሽ ሳር ልማትና ምንጭ ማጎልበት ዋና ዋና ስራዎች እንደነበሩ ጠቁመዋል፡፡


እስካሁንም 17ሺህ 141 ኪሎ ሜትር የእርከን እንዲሁም በጎርፍ የተሸረሸሩ የመሬት ክፍሎችን የማልማት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡


በተጨማሪም ለበጋ ወራት አገልግሎት የሚሰጡ ምንጮች መጎልበታቸውን፣ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች ዝግጅትም ጎን ለጎን ሲከናወን መቆየቱን ገልጸዋል።


ተፋሰሶቹን በእጽዋት በመሸፈን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ማዘጋጀትም የስራው አካል መሆኑን አመልክተዋል፡፡


በተፋሰስ ልማት ስራው ከ185ሺህ 200 በላይ ወጣቶች፣ ሴቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል፡፡


በተያያዘም በዘንድሮ የበጋ ወራት በዞኑ በሁሉም ወረዳዎች ከ11ሺህ ሄክታር በላይ የግጦሽ ሳር መሬት ከሰውና ከእንስሳት ንክኪ ተከልሏል ብለዋል፡፡


የተከለለው የግጦሽ ሳር ልማት በበጋ ወራት ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን ከ55ሺህ የሚበልጥ የቤት እንስሳትን ተጠቃሚ የማድረግ አቅም ያለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በዞኑ በድርቅ ተጋላጭ ከመሆን እና ከዝናብ እጥረት የሚያጋጥም የመኖ እጥረት በቤት እንስሳት ላይ ጉዳት እንደሚያደርስ አስታውሰዋል፡፡


ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ ችግሩን በዘላቂ ልማት ለመቋቋም በዞኑ ህዝብ ተሳትፎ የአፈርና ውሀ ጥበቃ ልማት ስራ በመካሄድ ላይ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025