የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ ፍትሃዊና የዜጎቿን የመጪው ዘመን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ነው

Jun 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ ፍትሃዊ፣ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥና የዜጎቿን የመጪው ዘመን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ነው ሲሉ ምሁራን ገለጹ።

ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ካሉ አገራት በርካታ የህዝብ ቁጥርና በፍጥነት እያደገ የሚገኝ ኢኮኖሚ ባለቤት ብትሆንም የባህር በር ባለቤት አለመሆኗ ዕድገቷ ከዚህ በላይ እንዳይሆን ተገዳድሮታል።

ጥናቶች እንደሚያመለክቱት የባህር በር ያላቸው አገራት ከሌላቸው አገራት በየዓመቱ የሁለት እስከ ሶስት በመቶ የምጣኔ ሀብት ዕድገት ያስመዘግባሉ።

በዚህም ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት አለመሆን በኢኮኖሚዋ ላይ ከፍተኛ ጫና ከመፍጠሩ ባለፈ ስትራቴጂካዊ ተጽዕኖ እንዳለው ይገለጻል።

በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ አማረ ቀናው (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የባህር በር ጥያቄ ጉዳይ ከኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በላይ ነው።

ለአንድ አገር ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ደህንነት መረጋገጥ የባህር በር ወሳኝና አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን ይጠቅሳሉ።

የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ ፍትሃዊ፣የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥና የዜጎቿን የመጪው ዘመን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ሰላማዊ መርህን ተከትላ ያቀረበችው የባህር በር ጥያቄ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ ዓለምአቀፍ ተቋማትና በፖሊሲ አውጪዎች አጽንኦት እየተሰጠው መምጣቱንም ነው ያነሱት።

ኢትዮጵያ ለቀይ ባህር ካላት ቅርበት አኳያ በዚያ አካባቢ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በትኩረት ትከታተላለች ብለዋል።

የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩትም በጉዳዩ ላይ በቂ ገንዛቤ በመፍጠር የመፍትሔ አማራጮችን በማመላከት በኩል ሲሰራ እንደቆየ አንስተዋል።

የኢትዮጵያ የፍትሃዊነትና የህልውና ጉዳይ የሆነው የባህር በር ጥያቄ በቅርቡ ምላሽ የሚያገኝበት ዕድሎች መኖራቸውንም ያብራራሉ።

በመሆኑን የጎረቤት አገራትን ጥቅም ባስከበረና የጋራ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ እንዲያገኝ ሰላማዊ የሆነ ግፊት ማድረጓን ትቀጥላለች ብለዋል።


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ጄይሉ ዑመር (ዶ/ር)፥ ኢትዮጵያ ሰጥቶ በመቀበል መርህ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ ማቅረቧ ተገቢና አዋጭ መሆኑን ተናግረዋል።

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጉዳዩ ምን ያህል ወሳኝ መሆኑን የሚያመላክቱ ሰነዶችን በጥናትና ምርምር ላይ ተመርኩዘው ማቅረብ አለባቸው ብለዋል።

ከዚያ ባለፈ ትውልዱ ስለ ጉዳዩ በቂ ዕውቀት እንዲኖረው የማስገንዘብ ሚናቸውን መወጣት አለባቸው ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከተለያዩ አገራት ጋር የምታደርገው የመሰረተ ልማት ትስስር የወደብ አማራጮችን ማስፋት ጉልህ ሚና እንዳለውም ነው ዶክተር አማረ የገለጹት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026