
አዲስ አበባ፤ሰኔ 5/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ ፍትሃዊ፣ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥና የዜጎቿን የመጪው ዘመን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ነው ሲሉ ምሁራን ገለጹ።
ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ካሉ አገራት በርካታ የህዝብ ቁጥርና በፍጥነት እያደገ የሚገኝ ኢኮኖሚ ባለቤት ብትሆንም የባህር በር ባለቤት አለመሆኗ ዕድገቷ ከዚህ በላይ እንዳይሆን ተገዳድሮታል።
ጥናቶች እንደሚያመለክቱት የባህር በር ያላቸው አገራት ከሌላቸው አገራት በየዓመቱ የሁለት እስከ ሶስት በመቶ የምጣኔ ሀብት ዕድገት ያስመዘግባሉ።
በዚህም ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት አለመሆን በኢኮኖሚዋ ላይ ከፍተኛ ጫና ከመፍጠሩ ባለፈ ስትራቴጂካዊ ተጽዕኖ እንዳለው ይገለጻል።
በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ አማረ ቀናው (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የባህር በር ጥያቄ ጉዳይ ከኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በላይ ነው።
ለአንድ አገር ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ደህንነት መረጋገጥ የባህር በር ወሳኝና አስፈላጊ ጉዳይ መሆኑን ይጠቅሳሉ።
የኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ ፍትሃዊ፣የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥና የዜጎቿን የመጪው ዘመን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ሰላማዊ መርህን ተከትላ ያቀረበችው የባህር በር ጥያቄ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ ዓለምአቀፍ ተቋማትና በፖሊሲ አውጪዎች አጽንኦት እየተሰጠው መምጣቱንም ነው ያነሱት።
ኢትዮጵያ ለቀይ ባህር ካላት ቅርበት አኳያ በዚያ አካባቢ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በትኩረት ትከታተላለች ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩትም በጉዳዩ ላይ በቂ ገንዛቤ በመፍጠር የመፍትሔ አማራጮችን በማመላከት በኩል ሲሰራ እንደቆየ አንስተዋል።
የኢትዮጵያ የፍትሃዊነትና የህልውና ጉዳይ የሆነው የባህር በር ጥያቄ በቅርቡ ምላሽ የሚያገኝበት ዕድሎች መኖራቸውንም ያብራራሉ።
በመሆኑን የጎረቤት አገራትን ጥቅም ባስከበረና የጋራ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ እንዲያገኝ ሰላማዊ የሆነ ግፊት ማድረጓን ትቀጥላለች ብለዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ጄይሉ ዑመር (ዶ/ር)፥ ኢትዮጵያ ሰጥቶ በመቀበል መርህ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ ማቅረቧ ተገቢና አዋጭ መሆኑን ተናግረዋል።
ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጉዳዩ ምን ያህል ወሳኝ መሆኑን የሚያመላክቱ ሰነዶችን በጥናትና ምርምር ላይ ተመርኩዘው ማቅረብ አለባቸው ብለዋል።
ከዚያ ባለፈ ትውልዱ ስለ ጉዳዩ በቂ ዕውቀት እንዲኖረው የማስገንዘብ ሚናቸውን መወጣት አለባቸው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከተለያዩ አገራት ጋር የምታደርገው የመሰረተ ልማት ትስስር የወደብ አማራጮችን ማስፋት ጉልህ ሚና እንዳለውም ነው ዶክተር አማረ የገለጹት።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026