የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ተወዳዳሪ ለማድረግ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል - ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር)

Jun 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2017(ኢዜአ)፦ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ተወዳዳሪ ለማድረግ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) ገለጹ።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ፣ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ከተሰማሩ ድርጅቶች ጋር ውይይት አካሂደዋል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በመድረኩ፤ የሀገርን የብልፅግና ጉዞ ለማፋጠን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን ቀልጣፋ ማድረግ የግድ ነው ብለዋል።


ዘርፉን ተወዳዳሪና ደህንነቱ የተጠበቀ ለማድረግ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አፅንኦት ሰጥተዋል።

የመርከብ አገልግሎት አሰጣጥን ከደንበኞች ፍላጎት ጋር ማጣጣምና የተጋነነ ዋጋ ካለ መፈተሽ ያስፈልጋል ነው ያሉት።

በዘርፉ የተሰማሩ ተቋማት አገልግሎታቸውን ለማሻሻል የሪፎርም ስራዎች እያከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰው፥ በዘርፉ ለብልሹ አሰራር የተጋለጡ ስራዎችን መፈተሽና ከሰው ንክኪ ነጻ የሆነ አሰራርን መተግበር እንደሚገባም ተናግረዋል።

በውይይቱ የተሳተፉ የሎጂስቲክስ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች በበኩላቸው፥ ከመርከብ አገልግሎት አሰጣጥ፣ ከጭነት ሚዛን ቁጥጥር፣ ከዋጋ ተወዳዳሪነትና ሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን አንስተዋል።

የዕቃ ማጓጓዣ ኮንቴነሮች እጥረት እንዲፈታና የመርከብ አገልግሎት ለማግኘት ፈጣን ምላሸ እየተሰጣቸው ባለመሆኑ እንዲስተካከል ጠይቀዋል።


የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ስራ አስፈጻሚ በሪሶ አመሎ(ዶ/ር)፥ አገልግሎት እየተሰጠ የሚገኘው በተቋሙ አሥር መርከቦችና ተጨማሪ መርከቦችን ደግሞ በመከራየት መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም በኪራይ የሚቀርቡ መርከቦችን ወደ አገልግሎት ለማሰማራት ጊዜ የሚፈጅ በመሆኑ ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር አንዱ ችግር ነው ብለዋል።

የዘርፉን አገልግሎት ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ መመሪያዎችን የማሻሻል ስራ እየተሰራ ነው ያሉት ዶክተር በሪሶ፥ በኦንላይን የተደገፈ አሰራር ሙሉ ለሙሉ በቅርቡ እንደሚጀመር ነው የገለጹት።

የመርከቦችን ቁጥር ለመጨመር የግዢ ሂደት ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍራኦል ጣፋ፥ አገልግሎት የሚሰጥባቸውን የመዳረሻ ሀገራት ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ሀብታሙ ሀይለሚካኤል በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስን የአገልግሎት አቅምና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማጎልበት እንዲሁም፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመደገፍ እንሰራለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025