የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ተወዳዳሪ ለማድረግ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል - ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር)

Jun 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2017(ኢዜአ)፦ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ተወዳዳሪ ለማድረግ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) ገለጹ።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ፣ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ከተሰማሩ ድርጅቶች ጋር ውይይት አካሂደዋል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በመድረኩ፤ የሀገርን የብልፅግና ጉዞ ለማፋጠን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን ቀልጣፋ ማድረግ የግድ ነው ብለዋል።


ዘርፉን ተወዳዳሪና ደህንነቱ የተጠበቀ ለማድረግ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አፅንኦት ሰጥተዋል።

የመርከብ አገልግሎት አሰጣጥን ከደንበኞች ፍላጎት ጋር ማጣጣምና የተጋነነ ዋጋ ካለ መፈተሽ ያስፈልጋል ነው ያሉት።

በዘርፉ የተሰማሩ ተቋማት አገልግሎታቸውን ለማሻሻል የሪፎርም ስራዎች እያከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰው፥ በዘርፉ ለብልሹ አሰራር የተጋለጡ ስራዎችን መፈተሽና ከሰው ንክኪ ነጻ የሆነ አሰራርን መተግበር እንደሚገባም ተናግረዋል።

በውይይቱ የተሳተፉ የሎጂስቲክስ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች በበኩላቸው፥ ከመርከብ አገልግሎት አሰጣጥ፣ ከጭነት ሚዛን ቁጥጥር፣ ከዋጋ ተወዳዳሪነትና ሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን አንስተዋል።

የዕቃ ማጓጓዣ ኮንቴነሮች እጥረት እንዲፈታና የመርከብ አገልግሎት ለማግኘት ፈጣን ምላሸ እየተሰጣቸው ባለመሆኑ እንዲስተካከል ጠይቀዋል።


የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ስራ አስፈጻሚ በሪሶ አመሎ(ዶ/ር)፥ አገልግሎት እየተሰጠ የሚገኘው በተቋሙ አሥር መርከቦችና ተጨማሪ መርከቦችን ደግሞ በመከራየት መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም በኪራይ የሚቀርቡ መርከቦችን ወደ አገልግሎት ለማሰማራት ጊዜ የሚፈጅ በመሆኑ ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር አንዱ ችግር ነው ብለዋል።

የዘርፉን አገልግሎት ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ መመሪያዎችን የማሻሻል ስራ እየተሰራ ነው ያሉት ዶክተር በሪሶ፥ በኦንላይን የተደገፈ አሰራር ሙሉ ለሙሉ በቅርቡ እንደሚጀመር ነው የገለጹት።

የመርከቦችን ቁጥር ለመጨመር የግዢ ሂደት ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍራኦል ጣፋ፥ አገልግሎት የሚሰጥባቸውን የመዳረሻ ሀገራት ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ሀብታሙ ሀይለሚካኤል በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስን የአገልግሎት አቅምና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማጎልበት እንዲሁም፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመደገፍ እንሰራለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026