
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2017(ኢዜአ)፦ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፉን ቀልጣፋና ተወዳዳሪ ለማድረግ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) ገለጹ።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ፣ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ከተሰማሩ ድርጅቶች ጋር ውይይት አካሂደዋል።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በመድረኩ፤ የሀገርን የብልፅግና ጉዞ ለማፋጠን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን ቀልጣፋ ማድረግ የግድ ነው ብለዋል።

ዘርፉን ተወዳዳሪና ደህንነቱ የተጠበቀ ለማድረግ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አፅንኦት ሰጥተዋል።
የመርከብ አገልግሎት አሰጣጥን ከደንበኞች ፍላጎት ጋር ማጣጣምና የተጋነነ ዋጋ ካለ መፈተሽ ያስፈልጋል ነው ያሉት።
በዘርፉ የተሰማሩ ተቋማት አገልግሎታቸውን ለማሻሻል የሪፎርም ስራዎች እያከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰው፥ በዘርፉ ለብልሹ አሰራር የተጋለጡ ስራዎችን መፈተሽና ከሰው ንክኪ ነጻ የሆነ አሰራርን መተግበር እንደሚገባም ተናግረዋል።
በውይይቱ የተሳተፉ የሎጂስቲክስ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች በበኩላቸው፥ ከመርከብ አገልግሎት አሰጣጥ፣ ከጭነት ሚዛን ቁጥጥር፣ ከዋጋ ተወዳዳሪነትና ሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን አንስተዋል።
የዕቃ ማጓጓዣ ኮንቴነሮች እጥረት እንዲፈታና የመርከብ አገልግሎት ለማግኘት ፈጣን ምላሸ እየተሰጣቸው ባለመሆኑ እንዲስተካከል ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዋና ስራ አስፈጻሚ በሪሶ አመሎ(ዶ/ር)፥ አገልግሎት እየተሰጠ የሚገኘው በተቋሙ አሥር መርከቦችና ተጨማሪ መርከቦችን ደግሞ በመከራየት መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም በኪራይ የሚቀርቡ መርከቦችን ወደ አገልግሎት ለማሰማራት ጊዜ የሚፈጅ በመሆኑ ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር አንዱ ችግር ነው ብለዋል።
የዘርፉን አገልግሎት ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ መመሪያዎችን የማሻሻል ስራ እየተሰራ ነው ያሉት ዶክተር በሪሶ፥ በኦንላይን የተደገፈ አሰራር ሙሉ ለሙሉ በቅርቡ እንደሚጀመር ነው የገለጹት።
የመርከቦችን ቁጥር ለመጨመር የግዢ ሂደት ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍራኦል ጣፋ፥ አገልግሎት የሚሰጥባቸውን የመዳረሻ ሀገራት ለማስፋት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ ሀብታሙ ሀይለሚካኤል በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስን የአገልግሎት አቅምና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማጎልበት እንዲሁም፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለመደገፍ እንሰራለን ብለዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026