የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በጎንደር ከተማ እየተከናወነ ላለው የኮሪደር ልማት ሥራ ህብረተሰቡ በተለያየ መንገድ ድጋፉን አጠናክሮ ቀጥሏል

Jun 27, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ በጎንደር ከተማ እየተከናወነ ለሚገኘው የኮሪደር ልማት ሥራ ህብረተሰቡ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት አስተዋጽኦ ማበርከቱን የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አስታወቁ።

ምክትል ከንቲባዋ ወይዘሮ ደብሬ የኋላ ለኢዜአ እንደተናገሩት በህዝቡ የነቃ ተሳትፎና ድጋፍ የኮሪደር ልማቱን በአጭር ጊዜ ወደ ትግበራ በማስገባት ተጨባጭ አፈጻጸም ማምጣት ተችሏል፡፡


ህብረተሰቡ ለመጀመሪያና ለሁለተኛ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ በገንዘብ፣ በጉልበትና በእውቀት ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ገልጸዋል።

የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ፈጥኖ እንዲጠናቀቅና 2ኛው ዙር እንዲጀመር የነቃ ትብብር ማድረጉንም ነው ያስታወሱት።

የኮሪደር ልማት ሥራ ግቡን እንዲመታ ህብረተሰቡ በመንግስት በተሰጠው ዲዛይን መሰረት ሕንጻና መኖሪያ ቤቱን በራሱ ወጪ በማደስ፤ በመጠገንና ቀለም በመቀባት ለልማቱ ድጋፉን አሳይቷል ብለዋል።

በሁለተኛው ምዕራፍ እየተከናወነ ለሚገኘው የኮሪደር ልማት ሥራ በተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር በሀገር ውስጥና በውጪ የሚገኙ የአካባቢው ተወላጆችና ባለሀብቶች የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ምክትል ከንቲባዋ ተናግረዋል።


ከተማው አሁን ላይ ወደ ተሟላና አስተማማኝ ሰላም በመሸጋገሩ ተቀዛቅዞ የቆየው የከተማው የንግድ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃት አሳይቷል፡፡

ከፒያሳ ኮሌጅ ማዞሪያና አዘዞ አየር ማረፊያ የእግረኛና የብስክሌት መንገድ፣ የአረንጓዴ መናፈሻዎች እንዲሁም ሌሎች ግንባታዎችን አካቶ እየተከናወነ ያለው 2ኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

የኮሪደር ልማት ሥራው በምሽት ጭምር በመስራት የህዝቡን የሥራ ባህል መቀየሩን ገልጸው፣ ልማቱ ለበርካታ ወገኖች የሥራ ዕድል መፍጠር ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡

በተያዘው ሳምንት በጎንደር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከመላ ሀገሪቱ በተውጣጡ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችና አመራሮች መጎብኘቱ የሚታወስ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025