
ጎንደር፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ በጎንደር ከተማ እየተከናወነ ለሚገኘው የኮሪደር ልማት ሥራ ህብረተሰቡ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት አስተዋጽኦ ማበርከቱን የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አስታወቁ።
ምክትል ከንቲባዋ ወይዘሮ ደብሬ የኋላ ለኢዜአ እንደተናገሩት በህዝቡ የነቃ ተሳትፎና ድጋፍ የኮሪደር ልማቱን በአጭር ጊዜ ወደ ትግበራ በማስገባት ተጨባጭ አፈጻጸም ማምጣት ተችሏል፡፡

ህብረተሰቡ ለመጀመሪያና ለሁለተኛ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ በገንዘብ፣ በጉልበትና በእውቀት ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ገልጸዋል።
የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ፈጥኖ እንዲጠናቀቅና 2ኛው ዙር እንዲጀመር የነቃ ትብብር ማድረጉንም ነው ያስታወሱት።
የኮሪደር ልማት ሥራ ግቡን እንዲመታ ህብረተሰቡ በመንግስት በተሰጠው ዲዛይን መሰረት ሕንጻና መኖሪያ ቤቱን በራሱ ወጪ በማደስ፤ በመጠገንና ቀለም በመቀባት ለልማቱ ድጋፉን አሳይቷል ብለዋል።
በሁለተኛው ምዕራፍ እየተከናወነ ለሚገኘው የኮሪደር ልማት ሥራ በተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር በሀገር ውስጥና በውጪ የሚገኙ የአካባቢው ተወላጆችና ባለሀብቶች የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ምክትል ከንቲባዋ ተናግረዋል።

ከተማው አሁን ላይ ወደ ተሟላና አስተማማኝ ሰላም በመሸጋገሩ ተቀዛቅዞ የቆየው የከተማው የንግድ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃት አሳይቷል፡፡
ከፒያሳ ኮሌጅ ማዞሪያና አዘዞ አየር ማረፊያ የእግረኛና የብስክሌት መንገድ፣ የአረንጓዴ መናፈሻዎች እንዲሁም ሌሎች ግንባታዎችን አካቶ እየተከናወነ ያለው 2ኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
የኮሪደር ልማት ሥራው በምሽት ጭምር በመስራት የህዝቡን የሥራ ባህል መቀየሩን ገልጸው፣ ልማቱ ለበርካታ ወገኖች የሥራ ዕድል መፍጠር ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡
በተያዘው ሳምንት በጎንደር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከመላ ሀገሪቱ በተውጣጡ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችና አመራሮች መጎብኘቱ የሚታወስ ነው፡፡
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026