
ጎንደር፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ በጎንደር ከተማ እየተከናወነ ለሚገኘው የኮሪደር ልማት ሥራ ህብረተሰቡ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት አስተዋጽኦ ማበርከቱን የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አስታወቁ።
ምክትል ከንቲባዋ ወይዘሮ ደብሬ የኋላ ለኢዜአ እንደተናገሩት በህዝቡ የነቃ ተሳትፎና ድጋፍ የኮሪደር ልማቱን በአጭር ጊዜ ወደ ትግበራ በማስገባት ተጨባጭ አፈጻጸም ማምጣት ተችሏል፡፡

ህብረተሰቡ ለመጀመሪያና ለሁለተኛ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ በገንዘብ፣ በጉልበትና በእውቀት ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ገልጸዋል።
የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ፈጥኖ እንዲጠናቀቅና 2ኛው ዙር እንዲጀመር የነቃ ትብብር ማድረጉንም ነው ያስታወሱት።
የኮሪደር ልማት ሥራ ግቡን እንዲመታ ህብረተሰቡ በመንግስት በተሰጠው ዲዛይን መሰረት ሕንጻና መኖሪያ ቤቱን በራሱ ወጪ በማደስ፤ በመጠገንና ቀለም በመቀባት ለልማቱ ድጋፉን አሳይቷል ብለዋል።
በሁለተኛው ምዕራፍ እየተከናወነ ለሚገኘው የኮሪደር ልማት ሥራ በተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር በሀገር ውስጥና በውጪ የሚገኙ የአካባቢው ተወላጆችና ባለሀብቶች የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውንም ምክትል ከንቲባዋ ተናግረዋል።

ከተማው አሁን ላይ ወደ ተሟላና አስተማማኝ ሰላም በመሸጋገሩ ተቀዛቅዞ የቆየው የከተማው የንግድ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃት አሳይቷል፡፡
ከፒያሳ ኮሌጅ ማዞሪያና አዘዞ አየር ማረፊያ የእግረኛና የብስክሌት መንገድ፣ የአረንጓዴ መናፈሻዎች እንዲሁም ሌሎች ግንባታዎችን አካቶ እየተከናወነ ያለው 2ኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
የኮሪደር ልማት ሥራው በምሽት ጭምር በመስራት የህዝቡን የሥራ ባህል መቀየሩን ገልጸው፣ ልማቱ ለበርካታ ወገኖች የሥራ ዕድል መፍጠር ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡
በተያዘው ሳምንት በጎንደር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከመላ ሀገሪቱ በተውጣጡ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችና አመራሮች መጎብኘቱ የሚታወስ ነው፡፡
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026