የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ኢትዮጵያ በአፍሪካ አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲዋን ማጠናከር የሚያስችል ውጤታማ ተሳትፎ አድርጋለች

Jun 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ በአንጎላ አዘጋጅነት በተካሄደው የአፍሪካ አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲዋን የሚያጠናክር ውጤታማ ተሳትፎ ማድረጓን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ።

17ኛው የአፍሪካ አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ በትናንትናው ዕለት ተጠናቋል።

ጉባኤው ኢትዮጵያ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጋር የተሰናሰነውን የቢዝነስ ዲፕሎማሲዋን ያጠናከረችበት መሆኑን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ዘርይሁን አበበ ለኢዜአ ገልጸዋል።


በጉባኤው የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ውጤታማ የሁለትዮሽ ውይይቶች ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

ከአንጎላው ፕሬዝዳንትና ከወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀ-መንበር ጆ ሌሬንሶ፤ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት የአፍሪካ ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቦሎስና የአፍሪካ ኮርፖሬት ካውንስል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሎሪ ሊዘር ጋር መወያየታቸውንም ጠቅሰዋል።

ከዋናው ጉባኤ ጎን ለጎን በነበሩ የተለያዩ መድረኮች ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴን ጨምሮ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ(ዶ/ር) እና በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) በኩል ተሳትፎ በማድረግ የኢትዮጵያን አቋም ማንጸባረቅ ተችሏል ብለዋል።

በዚህም በተለይም ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ምቹ መሆኗን ያሳየችባቸው፣ የዘርፉን የፖሊሲ ማዕቀፍ ያስተዋወቀችበት፣ የአፍሪካና የአሜሪካ የቢዝነስ ትስስር ምን መምሰል እንዳለበት እይታዋን ያካፈለችባቸው መድረኮች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እና በአሜሪካ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ትብብር መካከል የተፈረመው የመግባቢያ ሥምምነትም ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ የጀመረቻቸውን ሰፋፊ ጥረቶች ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑን አብራርተዋል።

ሥምምነቱ ከሁለት መቶ ሚሊየን ዶላር በላይ የኢንቨስትመንት ካፒታል የያዘ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም ኢትዮጵያ የቱርዝም መሰረተ ልማት በማስፋፋትና መዳረሻ ቦታዎችን በማልማት ምቹ ለማድረግ የያዘችውን ውጥን የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።

በተጓዳኝም፤ በጉባኤው የተለያዩ የግንኙነት መረቦች መዘርጋታቸውንም አምባሳደሩ ጨምረው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ልዑክ በዚህ ጉባኤ ላይ መሳተፉ ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በማሰናሰን ኢትዮጵያ ለቢዝነስ ዲፕሎማሲ የሰጠችውን ትኩረት የሚያሳይ መሆኑንም ገልጸዋል።

አምባሳደሩ አክለውም ጉባኤው የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ጥረቶች ለማጠናከር ዕድል የፈጠረ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ጉባኤው በዋናነት ለኢትዮጵያ ምርቶች ገበያ በማፈላለግ፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል በማስፋትና፣ የኢንቨስትመንት መዳረሻዎችን በማፈላለግና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ለመሳብ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል።

የዘንድሮው የአፍሪካ-አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ አሜሪካ በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአስተዳደር ዘመን አፍሪካን በተመለከተ የምትከተለው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ድጋፍን መሰረት ካደረገው ወደ ቢዝነስ ዲፕሎማሲ እንዲሸጋገር የተወሰነውን ውሳኔ ተከትሎ መካሄዱ ልዩ አድርጎታል።

ኢትዮጵያ 10ኛውን የአፍሪካ-አሜሪካ ጉባኤ ማዘጋጀቷ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025