የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወትን የበለጠ ጥቅም ላይ ለማዋል በትብብር መስራት ይገባል-ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)

Jun 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ካላት ብዝሃ ህይወት ህዝቦቿን የምትጠቅምበት እና ድህነትን የምታሸንፍበት መንገድ ለማድረግ በትብብር መስራት እንደሚገባ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለፁ።

የኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት እያከናወነ ያለውን ስራና ቀጣይ አቅጣጫ በተመለከተ ከክልል ቢሮ ኃላፊዎች ጋር ውይይት እያካሄደ ይገኛል።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት ኢትዮጵያ ብዝሀ ህይወትን ጨምሮ የበርካታ ሀብትና ፀጋ ባለቤት ነች።

ኢትዮጵያ ከ 6 ሺህ በላይ የእፅዋትና 7ሺህ በላይ የእንስሳት ዝርያ እንዳላትና ከዚህ ውስጥም 10 በመቶ ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ያለንን ብዝሃ ህይወት ጠቀሜታን ማወቅና መጠበቅ እንዲሁም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።

ብዝሃ ህይወት ለምግብና ለመድኃኒትነት እንዲሁም የተለያዩ ጥቅሞች ያሉት መሆኑን ገልፀው፤ ከሰው አኗኗርና ደህንነት ጋር የተያያዘ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በአየር ንብረት ለውጥና በተለያዩ ሰው ሰራሽ ምክንያቶች ብዝሀ ህይወት የመመናመንና የመጥፋት አደጋ እንደሚጋረጥበት ተናግረዋል።

አረንጓዴ አሻራ፣ አፈር ጥበቃና ሌሎች ስራዎች ለብዝሀ ህይወት ጥበቃ አስተዋጽኦ እንዳላቸውም ገልጸዋል።

የብዝሀ ህይወት ለስራ እድል፣ ለማህበራዊና ኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ጠቁመው፤ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ የድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ካላት ብዝሃ ህይወት ህዝቦቿን የምትጠቅምበትና ድህነትን የምታሸንፍበት መንገድ ለማድረግ በትብብር መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026