የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወትን የበለጠ ጥቅም ላይ ለማዋል በትብብር መስራት ይገባል-ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)

Jun 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 19/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ካላት ብዝሃ ህይወት ህዝቦቿን የምትጠቅምበት እና ድህነትን የምታሸንፍበት መንገድ ለማድረግ በትብብር መስራት እንደሚገባ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለፁ።

የኢትዮጵያ ብዝሃ ህይወት ኢንስቲትዩት እያከናወነ ያለውን ስራና ቀጣይ አቅጣጫ በተመለከተ ከክልል ቢሮ ኃላፊዎች ጋር ውይይት እያካሄደ ይገኛል።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት ኢትዮጵያ ብዝሀ ህይወትን ጨምሮ የበርካታ ሀብትና ፀጋ ባለቤት ነች።

ኢትዮጵያ ከ 6 ሺህ በላይ የእፅዋትና 7ሺህ በላይ የእንስሳት ዝርያ እንዳላትና ከዚህ ውስጥም 10 በመቶ ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ያለንን ብዝሃ ህይወት ጠቀሜታን ማወቅና መጠበቅ እንዲሁም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።

ብዝሃ ህይወት ለምግብና ለመድኃኒትነት እንዲሁም የተለያዩ ጥቅሞች ያሉት መሆኑን ገልፀው፤ ከሰው አኗኗርና ደህንነት ጋር የተያያዘ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በአየር ንብረት ለውጥና በተለያዩ ሰው ሰራሽ ምክንያቶች ብዝሀ ህይወት የመመናመንና የመጥፋት አደጋ እንደሚጋረጥበት ተናግረዋል።

አረንጓዴ አሻራ፣ አፈር ጥበቃና ሌሎች ስራዎች ለብዝሀ ህይወት ጥበቃ አስተዋጽኦ እንዳላቸውም ገልጸዋል።

የብዝሀ ህይወት ለስራ እድል፣ ለማህበራዊና ኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ጠቁመው፤ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ የድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ካላት ብዝሃ ህይወት ህዝቦቿን የምትጠቅምበትና ድህነትን የምታሸንፍበት መንገድ ለማድረግ በትብብር መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026