
አዳማ ፤ ሰኔ 19/2017( ኢዜአ) በኦሮሚያ ክልል በትራንስፖርት ዘርፉ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችንና ሌብነትን ለማስወገድ በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት እየተስፋፋ እንደሚገኝ የክልሉ ትራንስፖርት ኤጀንሲ ገለፀ።
በዘርፉ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል በሚደረገው ንቅናቄ ሙያተኞችና አመራሮች የድርሻቸውን እንዲወጡ በስነ-ምግባር ግንባታ ላይ ያተኮረ መድረክ በአዳማ ተካሄዷል።

የኦሮሚያ ትራንስፖርት ኤጀንሲ ምክትል ሃላፊ አቶ ለችሳ ሀዩ እንደገለፁት ኤጀንሲው በዘርፉ የሚስተዋል የሙስና፣ ብልሹ አሰራርና ሌብነትን ለማስወገድ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዲጂታል የአሰራር ስርዓት እየዘረጋ ነው።
በተለይ በዘርፉ የነበሩ የሌብነትና ብልሹ አሰራር ተጋላጭነትን ለመቀነስ የትራንስፖርት ስምሪት ዲጂታል በማድረግና አቅርቦቱን ለማሳለጥ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በዚህም በትራንስፖርት መናኸሪያዎች አገልግሎትን ዲጂታል ማድረግና የቁጥጥር ቴክኖሎጂን ማስፋፋት እንዲሁም አጠቃላይ አሰራር እንዲዘምን እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
አገልግሎቱን ከማዘመን ጎን ለጎን በስነ-ምግባር የታነጹ አስፈፃሚዎችና ፈፃሚዎችን ለማብዛት ከክልል ጀምሮ እስከ ታችኛው የአስተዳደር መዋቅር ድረስ ያሉ የትራንስፖርት ዘርፍ ሙያተኞችን የማነጽ ተግባርም እየተከናወነ ይገኛል ነው ያሉት።
በኤጀንሲው የትራፊክ ደህንነት ዳይሬክተር አቶ ሙስባሁዲን አብዱልመጅድ በበኩላቸው በዘርፉ ብልሹ አሰራርን ለመከላከል በተደረገ ጥረት 500 በየደረጃው ያሉ ሙያተኞች ላይ የተለያየ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።
በተወሰደው እርምጃም ተጠያቂነት የሰፈነበት አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽ ለማድረግ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል።

በተለይ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ማዕከላት ስልጠናና የመንጃ ፍቃድ ፈተና 'ኦንላይን' እንዲሆን የተደረገ ሲሆን '8556' ነፃ የስልክ መስመር በመጠቀም ህብረተሰቡ የሚያጋጥሙትን ችግሮች እንዲያጋልጥ አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም በትራንስፖርት መናኸሪያዎች ዲጂታል ቲኬት ላይ የአሽከርካሪው ሙሉ ስም፣ የተሽከርካሪ የሰሌዳ ቁጥርና ነፃ የስልክ መስመር ጭምር በማስገባት ሌብነትና ብልሹ አሰራርን የመከላከል ስራ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025