
አዳማ ፤ ሰኔ 19/2017( ኢዜአ) በኦሮሚያ ክልል በትራንስፖርት ዘርፉ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችንና ሌብነትን ለማስወገድ በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት እየተስፋፋ እንደሚገኝ የክልሉ ትራንስፖርት ኤጀንሲ ገለፀ።
በዘርፉ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል በሚደረገው ንቅናቄ ሙያተኞችና አመራሮች የድርሻቸውን እንዲወጡ በስነ-ምግባር ግንባታ ላይ ያተኮረ መድረክ በአዳማ ተካሄዷል።

የኦሮሚያ ትራንስፖርት ኤጀንሲ ምክትል ሃላፊ አቶ ለችሳ ሀዩ እንደገለፁት ኤጀንሲው በዘርፉ የሚስተዋል የሙስና፣ ብልሹ አሰራርና ሌብነትን ለማስወገድ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዲጂታል የአሰራር ስርዓት እየዘረጋ ነው።
በተለይ በዘርፉ የነበሩ የሌብነትና ብልሹ አሰራር ተጋላጭነትን ለመቀነስ የትራንስፖርት ስምሪት ዲጂታል በማድረግና አቅርቦቱን ለማሳለጥ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በዚህም በትራንስፖርት መናኸሪያዎች አገልግሎትን ዲጂታል ማድረግና የቁጥጥር ቴክኖሎጂን ማስፋፋት እንዲሁም አጠቃላይ አሰራር እንዲዘምን እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
አገልግሎቱን ከማዘመን ጎን ለጎን በስነ-ምግባር የታነጹ አስፈፃሚዎችና ፈፃሚዎችን ለማብዛት ከክልል ጀምሮ እስከ ታችኛው የአስተዳደር መዋቅር ድረስ ያሉ የትራንስፖርት ዘርፍ ሙያተኞችን የማነጽ ተግባርም እየተከናወነ ይገኛል ነው ያሉት።
በኤጀንሲው የትራፊክ ደህንነት ዳይሬክተር አቶ ሙስባሁዲን አብዱልመጅድ በበኩላቸው በዘርፉ ብልሹ አሰራርን ለመከላከል በተደረገ ጥረት 500 በየደረጃው ያሉ ሙያተኞች ላይ የተለያየ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።
በተወሰደው እርምጃም ተጠያቂነት የሰፈነበት አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽ ለማድረግ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል።

በተለይ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ማዕከላት ስልጠናና የመንጃ ፍቃድ ፈተና 'ኦንላይን' እንዲሆን የተደረገ ሲሆን '8556' ነፃ የስልክ መስመር በመጠቀም ህብረተሰቡ የሚያጋጥሙትን ችግሮች እንዲያጋልጥ አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም በትራንስፖርት መናኸሪያዎች ዲጂታል ቲኬት ላይ የአሽከርካሪው ሙሉ ስም፣ የተሽከርካሪ የሰሌዳ ቁጥርና ነፃ የስልክ መስመር ጭምር በማስገባት ሌብነትና ብልሹ አሰራርን የመከላከል ስራ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026