የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በኦሮሚያ ክልል በትራንስፖርት ዘርፉ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን ለማስወገድ በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት እየተስፋፋ ይገኛል

Jun 27, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤ ሰኔ 19/2017( ኢዜአ) በኦሮሚያ ክልል በትራንስፖርት ዘርፉ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችንና ሌብነትን ለማስወገድ በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት እየተስፋፋ እንደሚገኝ የክልሉ ትራንስፖርት ኤጀንሲ ገለፀ።

በዘርፉ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል በሚደረገው ንቅናቄ ሙያተኞችና አመራሮች የድርሻቸውን እንዲወጡ በስነ-ምግባር ግንባታ ላይ ያተኮረ መድረክ በአዳማ ተካሄዷል።


የኦሮሚያ ትራንስፖርት ኤጀንሲ ምክትል ሃላፊ አቶ ለችሳ ሀዩ እንደገለፁት ኤጀንሲው በዘርፉ የሚስተዋል የሙስና፣ ብልሹ አሰራርና ሌብነትን ለማስወገድ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዲጂታል የአሰራር ስርዓት እየዘረጋ ነው።

በተለይ በዘርፉ የነበሩ የሌብነትና ብልሹ አሰራር ተጋላጭነትን ለመቀነስ የትራንስፖርት ስምሪት ዲጂታል በማድረግና አቅርቦቱን ለማሳለጥ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም በትራንስፖርት መናኸሪያዎች አገልግሎትን ዲጂታል ማድረግና የቁጥጥር ቴክኖሎጂን ማስፋፋት እንዲሁም አጠቃላይ አሰራር እንዲዘምን እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

አገልግሎቱን ከማዘመን ጎን ለጎን በስነ-ምግባር የታነጹ አስፈፃሚዎችና ፈፃሚዎችን ለማብዛት ከክልል ጀምሮ እስከ ታችኛው የአስተዳደር መዋቅር ድረስ ያሉ የትራንስፖርት ዘርፍ ሙያተኞችን የማነጽ ተግባርም እየተከናወነ ይገኛል ነው ያሉት።

በኤጀንሲው የትራፊክ ደህንነት ዳይሬክተር አቶ ሙስባሁዲን አብዱልመጅድ በበኩላቸው በዘርፉ ብልሹ አሰራርን ለመከላከል በተደረገ ጥረት 500 በየደረጃው ያሉ ሙያተኞች ላይ የተለያየ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል።

በተወሰደው እርምጃም ተጠያቂነት የሰፈነበት አገልግሎት አሰጣጥ ተደራሽ ለማድረግ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አስረድተዋል።


በተለይ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ማዕከላት ስልጠናና የመንጃ ፍቃድ ፈተና 'ኦንላይን' እንዲሆን የተደረገ ሲሆን '8556' ነፃ የስልክ መስመር በመጠቀም ህብረተሰቡ የሚያጋጥሙትን ችግሮች እንዲያጋልጥ አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በትራንስፖርት መናኸሪያዎች ዲጂታል ቲኬት ላይ የአሽከርካሪው ሙሉ ስም፣ የተሽከርካሪ የሰሌዳ ቁጥርና ነፃ የስልክ መስመር ጭምር በማስገባት ሌብነትና ብልሹ አሰራርን የመከላከል ስራ ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025