የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማፍለቅ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው

Jun 27, 2025

IDOPRESS

ዲላ፤ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማፍለቅ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

የኢንስቲትዩቱ በምርምር ሥራዎች ላይ ያተኮረ የመጀመሪያው ዓመታዊ አውደ ጥናት በዲላ ከተማ ተካሂዷል።

በአውደ ጥናቱ ላይ ከ159 በላይ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ቀርበው የመጨረሻ ግምገማ መካሄዱም ተመላክቷል።

የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ያሲን ጎአ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢንስቲትዩቱ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማፍለቅ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው።


በተለይ በሰብል፣ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ እና በእንስሳት ልማት የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ የማስተዋወቅና የማስፋት ሥራ ትኩረት ሰጥቶ እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም የግብርና ምርታማነትንና የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መቻሉን ነው የገለጹት።

በአውደ ጥናቱ ከ159 በላይ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ለመጨረሻ ግምገማ መቅረባቸውንና የተመረጡትንም ለአርሶ አደሩ የማሸጋገር ሥራ እንደሚከናወን ገልጸዋል።

ኢንስቲትዩቱ በእንሰትና ሥራስር ሰብሎች የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ በማስተላለፍ ምርታማነትን ማሳደጉን የገለጹት ደግሞ የአረካ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ገነነ ገዛኸኝ ናቸው።


በተለይ በሽታን ተቋቁሞ በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጥ የቆላ የእንሰት ዝርያን በማስተዋወቅ በክልሉ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ መሆኑን አመልክተዋል።

በሙከራ ላይ የሚገኙ የእንሰት ማቀነባበሪያና መፋቂያ ቴክኖሎጂዎችን ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፣ ለእዚህም የአውደ ጥናቱ እገዛ የጎላ ነው ብለዋል።

የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ተክሌ ዮሴፍ በበኩላቸው፤ በማዕከሉ ለአርሶ አደሩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለማቅረብ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


በተያዘው ዓመት ተፈትሸው የወጡ የበቆሎ፣ ቦሎቄና ማሽላ ዝርያዎችን በማባዛትና በማስተዋወቅ የአርሶ አደሩና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውንም አስረድተዋል።

በተለይ ለተለያዩ ሥነ-ምህዳሮች ምቹ የሆኑ የሰብል ዝርያዎችን ከማስተዋወቅ ባለፈ ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ከእንስሳት ልማት ጋር የተያያዙ ስራዎችን በመስራት አርብቶ አደሩን በቅርበት እያገዙ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በአውደ ጥናቱ ላይ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና ከምርምር ማዕከላት የመጡ የተለያዩ ምሁራን ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026