ዲላ፤ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማፍለቅ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢንስቲትዩቱ በምርምር ሥራዎች ላይ ያተኮረ የመጀመሪያው ዓመታዊ አውደ ጥናት በዲላ ከተማ ተካሂዷል።
በአውደ ጥናቱ ላይ ከ159 በላይ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ቀርበው የመጨረሻ ግምገማ መካሄዱም ተመላክቷል።
የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ያሲን ጎአ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢንስቲትዩቱ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማፍለቅ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው።
በተለይ በሰብል፣ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ እና በእንስሳት ልማት የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ የማስተዋወቅና የማስፋት ሥራ ትኩረት ሰጥቶ እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም የግብርና ምርታማነትንና የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መቻሉን ነው የገለጹት።
በአውደ ጥናቱ ከ159 በላይ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ለመጨረሻ ግምገማ መቅረባቸውንና የተመረጡትንም ለአርሶ አደሩ የማሸጋገር ሥራ እንደሚከናወን ገልጸዋል።
ኢንስቲትዩቱ በእንሰትና ሥራስር ሰብሎች የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ በማስተላለፍ ምርታማነትን ማሳደጉን የገለጹት ደግሞ የአረካ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ገነነ ገዛኸኝ ናቸው።
በተለይ በሽታን ተቋቁሞ በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጥ የቆላ የእንሰት ዝርያን በማስተዋወቅ በክልሉ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ መሆኑን አመልክተዋል።
በሙከራ ላይ የሚገኙ የእንሰት ማቀነባበሪያና መፋቂያ ቴክኖሎጂዎችን ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፣ ለእዚህም የአውደ ጥናቱ እገዛ የጎላ ነው ብለዋል።
የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ተክሌ ዮሴፍ በበኩላቸው፤ በማዕከሉ ለአርሶ አደሩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለማቅረብ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በተያዘው ዓመት ተፈትሸው የወጡ የበቆሎ፣ ቦሎቄና ማሽላ ዝርያዎችን በማባዛትና በማስተዋወቅ የአርሶ አደሩና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውንም አስረድተዋል።
በተለይ ለተለያዩ ሥነ-ምህዳሮች ምቹ የሆኑ የሰብል ዝርያዎችን ከማስተዋወቅ ባለፈ ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ከእንስሳት ልማት ጋር የተያያዙ ስራዎችን በመስራት አርብቶ አደሩን በቅርበት እያገዙ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በአውደ ጥናቱ ላይ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና ከምርምር ማዕከላት የመጡ የተለያዩ ምሁራን ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025