የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማፍለቅ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው

Jun 27, 2025

IDOPRESS

ዲላ፤ሰኔ 19/2017 (ኢዜአ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማፍለቅ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

የኢንስቲትዩቱ በምርምር ሥራዎች ላይ ያተኮረ የመጀመሪያው ዓመታዊ አውደ ጥናት በዲላ ከተማ ተካሂዷል።

በአውደ ጥናቱ ላይ ከ159 በላይ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ቀርበው የመጨረሻ ግምገማ መካሄዱም ተመላክቷል።

የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ያሲን ጎአ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢንስቲትዩቱ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በምርምር በማፍለቅ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው።


በተለይ በሰብል፣ በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ እና በእንስሳት ልማት የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ የማስተዋወቅና የማስፋት ሥራ ትኩረት ሰጥቶ እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም የግብርና ምርታማነትንና የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ መቻሉን ነው የገለጹት።

በአውደ ጥናቱ ከ159 በላይ የግብርና ቴክኖሎጂዎች ለመጨረሻ ግምገማ መቅረባቸውንና የተመረጡትንም ለአርሶ አደሩ የማሸጋገር ሥራ እንደሚከናወን ገልጸዋል።

ኢንስቲትዩቱ በእንሰትና ሥራስር ሰብሎች የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ በማስተላለፍ ምርታማነትን ማሳደጉን የገለጹት ደግሞ የአረካ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ገነነ ገዛኸኝ ናቸው።


በተለይ በሽታን ተቋቁሞ በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርት የሚሰጥ የቆላ የእንሰት ዝርያን በማስተዋወቅ በክልሉ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት እያገዘ መሆኑን አመልክተዋል።

በሙከራ ላይ የሚገኙ የእንሰት ማቀነባበሪያና መፋቂያ ቴክኖሎጂዎችን ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፣ ለእዚህም የአውደ ጥናቱ እገዛ የጎላ ነው ብለዋል።

የጂንካ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ተክሌ ዮሴፍ በበኩላቸው፤ በማዕከሉ ለአርሶ አደሩ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለማቅረብ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


በተያዘው ዓመት ተፈትሸው የወጡ የበቆሎ፣ ቦሎቄና ማሽላ ዝርያዎችን በማባዛትና በማስተዋወቅ የአርሶ አደሩና አርብቶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውንም አስረድተዋል።

በተለይ ለተለያዩ ሥነ-ምህዳሮች ምቹ የሆኑ የሰብል ዝርያዎችን ከማስተዋወቅ ባለፈ ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና ከእንስሳት ልማት ጋር የተያያዙ ስራዎችን በመስራት አርብቶ አደሩን በቅርበት እያገዙ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በአውደ ጥናቱ ላይ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና ከምርምር ማዕከላት የመጡ የተለያዩ ምሁራን ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025