
ሰበታ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፡- በሸገር ከተማ አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።
በሸገር ከተማ አስተዳደር ፉሪ፣ ገላን ጉዳና ሰበታ ክፍለ ከተማዎች ከ11 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የከተማው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የከተማውን ነዋሪ ህዝብ ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክረው ቀጥለዋል።
ግንባታቸው የተጠናቀቁ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችም ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ ፕሮጀክቶቹ ከተማዋን የንግድ እና የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚያግዙ ናቸው ብለዋል።

የነዋሪውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን በማቃለል ተጠቃሚነቱን ይበልጥ የሚያረጋግጡ ናቸውም ብለዋል።
ዛሬ ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከልም የኮሪደር ልማት፣ ጤና ጣቢያዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች የተገነቡ መኖሪያ ቤቶች፣ መንገዶችና ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት ሌሎችም የልማት ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውንም አውስተዋል።
የከተማው ህዝብም የልማት ፕሮጀክቶቹ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ መንከባከብ እና መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል።
የፉሪ፣ ገላን ጉዳና ሰበታ ክፍለ ከተማ አስተዳደሮች በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቶቹ በመንግስት በጀትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ መገንባታቸውን ገልጸዋል።

ፕሮጀክቶቹ በክፍለ ከተሞቹ አስተዳደሮች የሚስተዋሉ የመሰረተ ልማቶችን እጥረት በዘላቂነት ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን የሚያግዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ፕሮጀክቶቹ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ከመፍታት በዘለለ በግንባታው ሂደት ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል የፈጠሩ እንደሆኑም አብራርተዋል።
ከከተማዋ ነዋሪዎችም ለአገልግሎት የበቁት የመሰረተ የልማት ፕሮጀክቶች የረጅም ጊዜ ጥያቄያቸውን የመለሱ መሆናቸውን በዚህም መደሰታቸውን ገልጸዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026