
ሰበታ፤ ሰኔ 21/2017(ኢዜአ)፡- በሸገር ከተማ አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።
በሸገር ከተማ አስተዳደር ፉሪ፣ ገላን ጉዳና ሰበታ ክፍለ ከተማዎች ከ11 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የከተማው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ የከተማውን ነዋሪ ህዝብ ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክረው ቀጥለዋል።
ግንባታቸው የተጠናቀቁ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችም ለአገልግሎት ክፍት እየተደረጉ መሆኑን ገልጸው፤ ፕሮጀክቶቹ ከተማዋን የንግድ እና የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚያግዙ ናቸው ብለዋል።

የነዋሪውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮችን በማቃለል ተጠቃሚነቱን ይበልጥ የሚያረጋግጡ ናቸውም ብለዋል።
ዛሬ ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከልም የኮሪደር ልማት፣ ጤና ጣቢያዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች የተገነቡ መኖሪያ ቤቶች፣ መንገዶችና ቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

እየተገባደደ ባለው በጀት ዓመት ሌሎችም የልማት ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውንም አውስተዋል።
የከተማው ህዝብም የልማት ፕሮጀክቶቹ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ መንከባከብ እና መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል።
የፉሪ፣ ገላን ጉዳና ሰበታ ክፍለ ከተማ አስተዳደሮች በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቶቹ በመንግስት በጀትና በህብረተሰቡ ተሳትፎ መገንባታቸውን ገልጸዋል።

ፕሮጀክቶቹ በክፍለ ከተሞቹ አስተዳደሮች የሚስተዋሉ የመሰረተ ልማቶችን እጥረት በዘላቂነት ለመፍታት የሚደረጉ ጥረቶችን የሚያግዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ፕሮጀክቶቹ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ከመፍታት በዘለለ በግንባታው ሂደት ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል የፈጠሩ እንደሆኑም አብራርተዋል።
ከከተማዋ ነዋሪዎችም ለአገልግሎት የበቁት የመሰረተ የልማት ፕሮጀክቶች የረጅም ጊዜ ጥያቄያቸውን የመለሱ መሆናቸውን በዚህም መደሰታቸውን ገልጸዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026