የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በኦሮሚያ ክልል ከለውጡ ዓመታት ወዲህ እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እያጎለበቱ ነው

Jul 1, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል ከለውጡ ዓመታት ወዲህ እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እያጎለበቱ መሆኑን የጨፌ ኦሮሚያ ምክትል አፈ ጉባዔ ኤልያስ ኡመታ አስታወቁ።

በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ከ2 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ የተገነቡ የልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

በዞኑ በተለያዩ ወረዳዎች የተገቡትን የልማት ፕሮጀክቶች የመረቁት የጨፌ ኦሮሚያ ምክትል አፈ ጉባዔ ኤልያስ ኡመታ እንደተናገሩት በክልሉ ከለውጡ ዓመታት ወዲህ የልማት ፕሮጀክቶች በስፋት እየተገነቡ ነው።


በክልሉ በተለያዩ ዞኖች እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች በጥራትና ፍጥነት ተጠናቀው ለአገልግሎት እየበቁ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ፕሮጀክቶቹም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እያጎለበቱ መሆኑን ጠቅሰው በዚህም የአመራሩ አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አመላክተዋል።

በዞኑ ከ2 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ የተገነቡ 310 ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃታቸውን የተናገሩት ደግሞ የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ሚስኪ መሀመድ ናቸው።


ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ለአገልግሎት መብቃታቸው በዞኑ ምርትና ምርታማነት ከማጎልበት ባለፈ በህዝቡ ዘንድ ሲነሳ የነበረውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ምላሽ የሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ ከ2014 ዓም ጀምሮ የ73 የመስኖ ግድብ ፕሮጀክት ስራ ተጀምሮ እስከ አሁን 33ቱን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉን የተናገሩት ደግሞ የኦሮሚያ ክልል መስኖና አርብቶ አደር ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ አለሙ ረጋሳ ናቸው።

ግድቦቹ ከመስኖ ልማት በተጨማሪ ለእንስሳት መጠጥ ውሃ፣ ለአሳ እርባታ፣ ለኢኮ ቱሪዝምና ለሌሎች አገልግሎት በማዋል ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ እየሰጡ መሆኑን ተናግረዋል።

በአካባቢያቸው ለእንስሳት መጠጥና ለመስኖ ልማት የሚሆን ውሀ ይቸግራቸው እንደነበር ያስታወሱት ደግሞ በዞኑ የጭናክሰን ወረዳ ነዋሪ ከፊል አርሶ አደር ኡስማኢል አህመድ ናቸው።


አሁን የተገነባው ግድብ ለነበረባቸው ችግር መፍትሄ የሰጠ መሆኑን ጠቁመው በተለይ ግድቡ ከመስኖ ልማት በተጨማሪ ለአሳ እርባታና ለሌሎች የልማት ስራዎች ከፍተኛ አገልግሎት የሚሰጥ በመሆኑ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

በቀበሌያቸው የተገነቡ የውሃ ፕሮጀክቶች ለከብቶቻችውና ለእርሻ ስራቸው ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በጭናክሰን ወረዳ የመረር ቀበሌ ነዋሪ ከፊል አርሶ አደር ሁሴን ዮኒስ ናቸው።

በምስራቅ ሐረርጌ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች የተገነቡ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት፣ ድልድዮች፣ የመስኖ ግድቦች፤ የአስተዳደር ህንጻዎችና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025