ወላይታ ሶዶ፤ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝቡን የመልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝግበዋል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተናገሩ።
"ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ ክልል አቀፍ የሠላም፣ የልማት እና የአንድነት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው።
ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፥ የክልሉን ህዝቡ የመልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ በተደረጉ ጥረቶች በኢኮኖሚው ፣ በማህበራዊና በፖለቲካው ዘርፎች ስኬቶች ተመዝግበዋል።
የልማት ስራዎቹ የህብረተሰቡ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ያገናዘቡ እንዲሆኑ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል።
የመንግስት ተቋማት ሽፋንና የአገልግሎት ተደራሽነትን በማሳደግ የተገልጋዩን እርካታ ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ለውጦች መታየታቸውን አንስተዋል።
የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በበኩላቸው፥ ክልሉ ከተደራጀ ጊዜ አንስቶ የሕዝቡን ሁለንተናዊ ጥያቄዎች ለመመለስ በተሰራው ስራ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
የፖለቲካ እሳቤን በማዘመን የህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ዕሴትን በማስረጽ በኩልም ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን አብራርተዋል።
የውይይቱ ተሳታፊ የሆኑት አቶ ያዕቆብ አልታዬ በበኩላቸው፥ በክልሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ የመጣውን ለውጥ ለማስቀጠል ተባብሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።
ለዚህ ደግሞ የአመራር ቁርጠኝነትና የህዝቡ ትብብር አስፈላጊ በመሆኑ በቅንጅት መስራት አስፈላጊ ነው ብለዋል ።
''ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ያለው ክልል አቀፍ የሠላም፣ የልማት እና የአንድነት ኮንፈረንስ ነገም ቀጥሎ እንደሚካሄድ ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025