
ወላይታ ሶዶ፤ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝቡን የመልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝግበዋል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተናገሩ።
"ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ ክልል አቀፍ የሠላም፣ የልማት እና የአንድነት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፥ የክልሉን ህዝቡ የመልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ በተደረጉ ጥረቶች በኢኮኖሚው ፣ በማህበራዊና በፖለቲካው ዘርፎች ስኬቶች ተመዝግበዋል።
የልማት ስራዎቹ የህብረተሰቡ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ያገናዘቡ እንዲሆኑ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል።
የመንግስት ተቋማት ሽፋንና የአገልግሎት ተደራሽነትን በማሳደግ የተገልጋዩን እርካታ ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ለውጦች መታየታቸውን አንስተዋል።
የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በበኩላቸው፥ ክልሉ ከተደራጀ ጊዜ አንስቶ የሕዝቡን ሁለንተናዊ ጥያቄዎች ለመመለስ በተሰራው ስራ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
የፖለቲካ እሳቤን በማዘመን የህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ዕሴትን በማስረጽ በኩልም ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን አብራርተዋል።
የውይይቱ ተሳታፊ የሆኑት አቶ ያዕቆብ አልታዬ በበኩላቸው፥ በክልሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ የመጣውን ለውጥ ለማስቀጠል ተባብሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።
ለዚህ ደግሞ የአመራር ቁርጠኝነትና የህዝቡ ትብብር አስፈላጊ በመሆኑ በቅንጅት መስራት አስፈላጊ ነው ብለዋል ።
''ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ያለው ክልል አቀፍ የሠላም፣ የልማት እና የአንድነት ኮንፈረንስ ነገም ቀጥሎ እንደሚካሄድ ተገልጿል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026