የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የህዝቡን የመልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝግበዋል

Jul 1, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ሰኔ 23/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝቡን የመልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝግበዋል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ተናገሩ።

"ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ ክልል አቀፍ የሠላም፣ የልማት እና የአንድነት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው።


ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፥ የክልሉን ህዝቡ የመልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ በተደረጉ ጥረቶች በኢኮኖሚው ፣ በማህበራዊና በፖለቲካው ዘርፎች ስኬቶች ተመዝግበዋል።

የልማት ስራዎቹ የህብረተሰቡ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ያገናዘቡ እንዲሆኑ ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል።

የመንግስት ተቋማት ሽፋንና የአገልግሎት ተደራሽነትን በማሳደግ የተገልጋዩን እርካታ ለማረጋገጥ በተከናወኑ ተግባራት ለውጦች መታየታቸውን አንስተዋል።

የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በበኩላቸው፥ ክልሉ ከተደራጀ ጊዜ አንስቶ የሕዝቡን ሁለንተናዊ ጥያቄዎች ለመመለስ በተሰራው ስራ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

የፖለቲካ እሳቤን በማዘመን የህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነት እና እህትማማችነት ዕሴትን በማስረጽ በኩልም ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን አብራርተዋል።

የውይይቱ ተሳታፊ የሆኑት አቶ ያዕቆብ አልታዬ በበኩላቸው፥ በክልሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ የመጣውን ለውጥ ለማስቀጠል ተባብሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

ለዚህ ደግሞ የአመራር ቁርጠኝነትና የህዝቡ ትብብር አስፈላጊ በመሆኑ በቅንጅት መስራት አስፈላጊ ነው ብለዋል ።

''ጠንካራ ክልላዊ አንድነትና አብሮነት ለዘላቂ ሠላምና ብልጽግና" በሚል መሪ ሃሳብ በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ያለው ክልል አቀፍ የሠላም፣ የልማት እና የአንድነት ኮንፈረንስ ነገም ቀጥሎ እንደሚካሄድ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025