ጊምቢ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል ከተሞች የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች የሚመልሱ የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን በክልሉ በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የከተማ ልማት አስተባባሪ አቶ መስፍን መላኩ ገለጹ።
በምዕራብ ወለጋ ዞን ዪብዶ ወረዳ ግንባታቸው የተጠናቀቁ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ተቋማት የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።
ተመርቀው ለአገልግሎት ከበቁ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች መካከል የወጣቶች ማዕከል፣ 'ዪብዶ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት እና ሌሎች ይገኙበታል።
በመሰረተ ልማት ተቋማቱ ምረቃ ላይ በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የከተማ ልማት አስተባባሪ አቶ መስፍን መላኩ፣ በክልሉ ከተሞች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ በስፋት እየተካሄደ ነው።
የክልሉ መንግሥት ከለውጡ በኋላ የህዝቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ስራዎችን በትኩረት እያከናወነ መሆኑን ገልጸው የመሰረተ ልማት ተቋማት ደግሞ ስፊውን ድርሻ ይዘዋል ብለዋል።
በክልሉ ከተሞች በበጀት ዓመቱ ግንባታቸው ሲከናወን የቆዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ሰሞኑን ተመርቀው ለአገልግሎት እየበቁ እንደሚገኙም አመልክተዋል።
በቀጣይም በከተሞች የህዝቡን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ ይጠናከራል ብለዋል።
በተለይም በምዕራብ ወለጋ ዞን ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቁ የመሰረተ ልማት ተቋማት የአካባቢውን ልማት የሚያነቃቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በዞኑ ተስፋ ሰጪ የልማት እንቅስቃሴ እየታየ መምጣቱን ጠቅሰው ህዝቡም ከየትኛውም ጊዜ በላይ የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የምዕራብ ወለጋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፈ በበኩላቸው በዞኑ ዘላቂ ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎን የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የአጭር እና የረጅም ጊዜ እቅድ ተዘጋጅቶ እየተተገበረ ይገኛል ብለዋል።
በዛሬው እለትም ከ249 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ የመሰረተ ልማት ተቋማት ለህዝብ አገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ገልጸዋል።
መንግስት የመልካም አስተዳደር ችግር መነሻ የሆኑ ጉዳዮችን ለይቶ መፍትሄ ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስረድተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025