
ጊምቢ፤ ሰኔ 25/2017(ኢዜአ)፡-በኦሮሚያ ክልል ከተሞች የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች የሚመልሱ የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን በክልሉ በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የከተማ ልማት አስተባባሪ አቶ መስፍን መላኩ ገለጹ።
በምዕራብ ወለጋ ዞን ዪብዶ ወረዳ ግንባታቸው የተጠናቀቁ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ተቋማት የክልሉ መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።

ተመርቀው ለአገልግሎት ከበቁ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች መካከል የወጣቶች ማዕከል፣ 'ዪብዶ ኢፋ ቦሩ ትምህርት ቤት እና ሌሎች ይገኙበታል።
በመሰረተ ልማት ተቋማቱ ምረቃ ላይ በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የከተማ ልማት አስተባባሪ አቶ መስፍን መላኩ፣ በክልሉ ከተሞች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ በስፋት እየተካሄደ ነው።

የክልሉ መንግሥት ከለውጡ በኋላ የህዝቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችሉ ስራዎችን በትኩረት እያከናወነ መሆኑን ገልጸው የመሰረተ ልማት ተቋማት ደግሞ ስፊውን ድርሻ ይዘዋል ብለዋል።
በክልሉ ከተሞች በበጀት ዓመቱ ግንባታቸው ሲከናወን የቆዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ሰሞኑን ተመርቀው ለአገልግሎት እየበቁ እንደሚገኙም አመልክተዋል።
በቀጣይም በከተሞች የህዝቡን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ተቋማት ግንባታ ይጠናከራል ብለዋል።

በተለይም በምዕራብ ወለጋ ዞን ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት የበቁ የመሰረተ ልማት ተቋማት የአካባቢውን ልማት የሚያነቃቁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በዞኑ ተስፋ ሰጪ የልማት እንቅስቃሴ እየታየ መምጣቱን ጠቅሰው ህዝቡም ከየትኛውም ጊዜ በላይ የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የምዕራብ ወለጋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፈ በበኩላቸው በዞኑ ዘላቂ ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎን የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የአጭር እና የረጅም ጊዜ እቅድ ተዘጋጅቶ እየተተገበረ ይገኛል ብለዋል።

በዛሬው እለትም ከ249 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ የመሰረተ ልማት ተቋማት ለህዝብ አገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን ገልጸዋል።
መንግስት የመልካም አስተዳደር ችግር መነሻ የሆኑ ጉዳዮችን ለይቶ መፍትሄ ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስረድተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025