🔇Unmute
ሀዋሳ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል በበጀት ዓመቱ ከ40 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ እንደሚቀርብ የክልሉ ቡና ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ገለፀ ።
ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ እንደገለፁት በተያዘው በጀት ዓመት 40 ሺህ 169 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ ይገኛል፡፡
ከዚህ ውስጥ 85 በመቶ የሚሆነው የታጠበ ቡና ሲሆን ቀሪው ያልታጠበ እንደሚሆን አቶ መስፍን ገልፀው እቅዱንም ለማሳካት የታጠበ ቡና ከሚያዘጋጁ 425 ኢንዱስትሪዎች መካከል 70 በመቶዎቹ ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል ፡፡

ኢንዱስትሪዎቹ ጥራት ያለው ቡናን እንዲያመርቱም የግንዛቤ፣ የድጋፍና ክትትል ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመዋል፡፡
ቡናን ከአርሶ አደሩ በሚረከቡበት ወቅት እሸቱን ብቻ በመቀበል የጥራት ደረጃውን ማስጠበቅ ላይ እንዲያተኩሩ መሰራቱን አስረድተዋል፡፡
የቡና ግብይቱን ጤናማነት ለማረጋገጥ ህገወጥ የምርት ዝውውርን ለመቆጣጠር እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ የጋራ ግብረ ኃይል መዋቀሩን ገልፀዋል፡፡
በክልሉ ከ401 ሺህ በላይ የሚሆኑ አርሶ አደሮች በቡና ምርት ላይ የተሰማሩ መሆናቸውን ጠቅሰው አርሶ አደሩ ለኢንዱስትሪው የሚያቀርበው ቡና ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል ፡፡
የቡና ግብይትን ጤናማ ለማድረግ ከሚሰራው ስራ ጎን ለጎንም ምርታማነቱን ለማሳደግ ለአርሶ አደሩ የተሻሻሉ ዝርያዎች መቅረባቸውንና የባለሙያ ድጋፍ መደረጉን አክለዋል።
አርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ አጠቃቀምና ሌሎች የፓኬጅ ሥራዎችን ማሻሻል በመቻሉ በሄክታር የሚገኘው የምርት መጠንም እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰዋል፡፡

ለአብነትም ከዚህ በፊት በሄክታር የሚገኘው ቡና ከሰባት ኩንታል ያልበለጠ እንደነበር ጠቅሰው ባለፈው አመት 11 ነጥብ 04 ኩንታል በሄክታር ምርት ማግኘት እንደተቻለ አስረድተዋል፡፡
የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ 4 ነጥብ 4 ሚሊዮን ቶን የተፈጥሮ ማዳበሪያ ጥቅም ላይ መዋሉን ተናግረዋል ፡፡
የቡና ምርት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን ለማጉላት ጥራቱን የጠበቀ አመራረት፣ አሰባሰብና ግብይት እንዲኖር ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በቁርጠኝነት እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የቡና ምርት ብዛትና ጥራትን ለማስጠበቅ ባለፉት አምስት ዓመታት ክልሉ ባከናወነው ተግባርም ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርበውን የቡና መጠን ከ25 ሺህ ቶን ወደ 40 ሺህ ቶን ማሳደግ መቻሉን ከባለሥልጣኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025