🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ):- በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት እርባታን በማዘመን ህብረተሰቡ ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆን የተከናወነው ተግባር ውጤት ማምጣቱን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።
ሀገር አቀፍ የእንስሳት አርቢዎች ቀን በወላይታ ሶዶ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።
በወቅቱም የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር)፤ የእንስሳት እርባታን በማዘመን ህብረተሰቡ በሌማት ትሩፋት ተጠቃሚ እንዲሆን የተሰራው ስራ ውጤት አምጥቷል ብለዋል።

በወላይታ ሶዶ ከተማ በተካሄደ የእንስሳት እርባታ ጣቢያዎች የመስክ ምልከታ ላይ ተገኝተው በወተት ላም እርባታ ዘርፍ እየተከናወነ ያለው ተግባር የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አካል እንደሆነ በመጥቀስ እንቅስቃሴውም አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።
በመስክ ምልከታውም በሀገር አቀፍ ደረጃ የተውጣጡ የዘርፉ ተዋንያን እንዲሳተፉ መደረጉን ጠቁመው፤ በወላይታ ሶዶ ከተማ ያዩትን ተሞክሮ በመቀመር የተሻለ እንዲሰሩ ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።

በክልሉ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ በቁርጠኝነት እየተደረገ ያለው ድጋፍ ውጤት ማሳየቱን አመልክተዋል።
የክልሉን አርሶ እና አርብቶ አደሮችን ኑሮ ለማሻሻል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ናቸው።

በተቀናጀ መንገድ ዘርን በድጋፍ መልክ በማቅረብ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገባቸውን ጠቁመው፤ የወላይታ ሶዶ ከተማ እንስሳት አርቢዎች ያስመዘገቡት ውጤት የዚህ ማሳያና በትጋት የመጣ መሆኑን ተናግረዋል።
በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር መንግስት የጀመረውን ስራ በማጠናከር የወተት ፍላጎትን በበቂ ሁኔታ ለማሟላት በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል ።
በሁሉም የሌማት ትሩፋት ዘርፎች የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች አመርቂ መሆናቸውን ገልጸው፤ ከዘርፉ የሚገኘውን የኢኮኖሚ ትሩፋት ለሁሉም ለማዳረስ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አንስተዋል።

በወላይታ ሶዶ ከተማ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ በሚገኘው ሀገር አቀፍ የእንስሳት አርቢዎች ቀን ዝግጅት ላይ የፌዴራልና የክልል የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026