🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ):- በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት እርባታን በማዘመን ህብረተሰቡ ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆን የተከናወነው ተግባር ውጤት ማምጣቱን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።
ሀገር አቀፍ የእንስሳት አርቢዎች ቀን በወላይታ ሶዶ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።
በወቅቱም የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር)፤ የእንስሳት እርባታን በማዘመን ህብረተሰቡ በሌማት ትሩፋት ተጠቃሚ እንዲሆን የተሰራው ስራ ውጤት አምጥቷል ብለዋል።

በወላይታ ሶዶ ከተማ በተካሄደ የእንስሳት እርባታ ጣቢያዎች የመስክ ምልከታ ላይ ተገኝተው በወተት ላም እርባታ ዘርፍ እየተከናወነ ያለው ተግባር የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አካል እንደሆነ በመጥቀስ እንቅስቃሴውም አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።
በመስክ ምልከታውም በሀገር አቀፍ ደረጃ የተውጣጡ የዘርፉ ተዋንያን እንዲሳተፉ መደረጉን ጠቁመው፤ በወላይታ ሶዶ ከተማ ያዩትን ተሞክሮ በመቀመር የተሻለ እንዲሰሩ ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።

በክልሉ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ በቁርጠኝነት እየተደረገ ያለው ድጋፍ ውጤት ማሳየቱን አመልክተዋል።
የክልሉን አርሶ እና አርብቶ አደሮችን ኑሮ ለማሻሻል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ናቸው።

በተቀናጀ መንገድ ዘርን በድጋፍ መልክ በማቅረብ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገባቸውን ጠቁመው፤ የወላይታ ሶዶ ከተማ እንስሳት አርቢዎች ያስመዘገቡት ውጤት የዚህ ማሳያና በትጋት የመጣ መሆኑን ተናግረዋል።
በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር መንግስት የጀመረውን ስራ በማጠናከር የወተት ፍላጎትን በበቂ ሁኔታ ለማሟላት በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል ።
በሁሉም የሌማት ትሩፋት ዘርፎች የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች አመርቂ መሆናቸውን ገልጸው፤ ከዘርፉ የሚገኘውን የኢኮኖሚ ትሩፋት ለሁሉም ለማዳረስ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አንስተዋል።

በወላይታ ሶዶ ከተማ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ በሚገኘው ሀገር አቀፍ የእንስሳት አርቢዎች ቀን ዝግጅት ላይ የፌዴራልና የክልል የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026