የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት እርባታን በማዘመን ረገድ የተከናወነው ተግባር ውጤት አምጥቷል

Oct 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ):- በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የእንስሳት እርባታን በማዘመን ህብረተሰቡ ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆን የተከናወነው ተግባር ውጤት ማምጣቱን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።

ሀገር አቀፍ የእንስሳት አርቢዎች ቀን በወላይታ ሶዶ ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።

በወቅቱም የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር)፤ የእንስሳት እርባታን በማዘመን ህብረተሰቡ በሌማት ትሩፋት ተጠቃሚ እንዲሆን የተሰራው ስራ ውጤት አምጥቷል ብለዋል።


በወላይታ ሶዶ ከተማ በተካሄደ የእንስሳት እርባታ ጣቢያዎች የመስክ ምልከታ ላይ ተገኝተው በወተት ላም እርባታ ዘርፍ እየተከናወነ ያለው ተግባር የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አካል እንደሆነ በመጥቀስ እንቅስቃሴውም አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።

በመስክ ምልከታውም በሀገር አቀፍ ደረጃ የተውጣጡ የዘርፉ ተዋንያን እንዲሳተፉ መደረጉን ጠቁመው፤ በወላይታ ሶዶ ከተማ ያዩትን ተሞክሮ በመቀመር የተሻለ እንዲሰሩ ምሳሌ የሚሆን ነው ብለዋል።


በክልሉ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ በቁርጠኝነት እየተደረገ ያለው ድጋፍ ውጤት ማሳየቱን አመልክተዋል።

የክልሉን አርሶ እና አርብቶ አደሮችን ኑሮ ለማሻሻል በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) ናቸው።


በተቀናጀ መንገድ ዘርን በድጋፍ መልክ በማቅረብ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገባቸውን ጠቁመው፤ የወላይታ ሶዶ ከተማ እንስሳት አርቢዎች ያስመዘገቡት ውጤት የዚህ ማሳያና በትጋት የመጣ መሆኑን ተናግረዋል።

በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር መንግስት የጀመረውን ስራ በማጠናከር የወተት ፍላጎትን በበቂ ሁኔታ ለማሟላት በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል ።

በሁሉም የሌማት ትሩፋት ዘርፎች የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች አመርቂ መሆናቸውን ገልጸው፤ ከዘርፉ የሚገኘውን የኢኮኖሚ ትሩፋት ለሁሉም ለማዳረስ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አንስተዋል።


በወላይታ ሶዶ ከተማ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ በሚገኘው ሀገር አቀፍ የእንስሳት አርቢዎች ቀን ዝግጅት ላይ የፌዴራልና የክልል የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026