የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ-ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተሻሻለ የእንስሳት መኖን ለአካባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚሰራ አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው በ45 ሚሊዮን ብር ወጭ ያስገነባው የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ዛሬ ተመርቋል።


የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስማረ መለስ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው ጎን ለጎን የአካባቢውን ጸጋ መሰረት በማድረግ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎች እያከናወነ ይገኛል።

በተለይ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በእንስሳት እርባታ ዘርፍ የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ለዚህም ዩኒቨርሲቲው የተሻሻለ ዝርያ ያላቸው የወተት ላሞችን በማርባት በወተት አቅርቦት ራሱን ከመቻል ባለፈ የአካባቢው አርሶ አደሮች ሳይንሳዊ የእንስሳት እርባታ ላይ እንዲያተኩሩ እያከናወናቸው ያሉ ተግበራትን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

በአካባቢው በእንስሳት ርባታና ማድለብ ሥራ ምርታማነት ለማሳደግም በ45 ሚሊዮን ብር ወጭ ያስገነባውን የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ዛሬ ማስመረቁንም አስማረ (ዶ/ር) ተናግረዋል።


እንደእሳቸው ገለጻ ፋብሪካው በሰዓት ከ50 ኩንታል በላይ የመኖ ምርት በማምረት የወተትና የሥጋ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል ነው።

በዚህም ዩኒቨርሲቲው የተሻሻለ የእንስሳት መኖን ለአካባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ አርሶ አደሩን በዘላቂነት ተጠቃሚ ለማድረግ የጀመራቸውን ሥራዎች ያጠናክራል ብለዋል።

በቀጣይም የወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ማቀዱን ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል።

በአሁኑ ወቅትም ዩኒቨርሲቲው ባለ ሰባት እና ባለ ስድስት ወለል የመምህራን መኖሪያ ቤት ሕንጻዎችን እያስገነባ እንደሚገኝ የተናገሩት አስማረ (ዶ/ር) ፣ ሕንጻዎቹ ከመምህራን መኖሪያ ቤት በተጨማሪ ለንግድ፣ ለመዝናኛና የጋራ የማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ከፍሎችን አካተው እየተገነቡ መሆኑን አስረድተዋል።


የዩኒቨርሲቲው የቦርድ አባል ወይዘሮ መሰንበት ሸንቁጤ በበኩላቸው እንዳሉት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ወደ ራስ ገዝነት በመሸጋገር ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ሃይል ማምረት እንዳለባቸው አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሰራ ነው።


የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ እየተገበራቸው ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች የራሱን አቅም በማሳደግ በቀጣይ ወደ ራስ ገዝነት ለመሸጋገር የሚያስችሉ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

ዛሬ የተመረቀው የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካም የአካባቢውን የእንስሳት እርባታ ሥራ በመደገፍ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ ዩኒቨርሲቲው እያስገነባው ያለው የመምህራን መኖሪያ ቤት ሕንጻ በመምህራን ሲነሳ የነበረውን ችግር ለመፍታት ያስችላል ብለዋል።

በቀጣይ ከተማ አስተዳደሩ የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ከዩኒቨርሲቲው ጋር በትብብር እንደሚሰራ አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026