የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ ቡናን በብዛትና በጥራት በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ቦንጋ፣ ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቡናን በብዛትና በጥራት በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን አስታወቀ።

የክልሉ ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ለተለያዩ የዘርፉ ባለሙያዎችና የሚመለከታቸው አካላት የቡና አዘገጃጀትና ጥራት ማስጠበቅ ላይ ያተኮረ ስልጠና እየሰጠ ነው።


በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር የደረጉት የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አስራት መኩሪያ፤ በክልሉ ከቡና ልማትና ምርታማነት በተጨማሪ ለጥራት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።

የቡና ምርትና ጥራት የሚረጋገጠው በሁሉም ጥረትና ትብብር ቢሆንም በተለይም የባለሙያዎች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህም መሰረት የቡና ምርት ዝግጅትና ግብይት ሂደት የተሳለጠ እና ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን የባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻዎችን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በክልሉ ቡናን በብዛትና በጥራት በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።

በመሆኑም የቡና አምራቾችና የመፈልፈያ ኢንዱስትሪ ባለቤቶችና አርሶ አደሮች ለቡና ምርት ጥራት ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025