🔇Unmute
ቦንጋ፣ ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቡናን በብዛትና በጥራት በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን አስታወቀ።
የክልሉ ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ለተለያዩ የዘርፉ ባለሙያዎችና የሚመለከታቸው አካላት የቡና አዘገጃጀትና ጥራት ማስጠበቅ ላይ ያተኮረ ስልጠና እየሰጠ ነው።

በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር የደረጉት የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አስራት መኩሪያ፤ በክልሉ ከቡና ልማትና ምርታማነት በተጨማሪ ለጥራት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።
የቡና ምርትና ጥራት የሚረጋገጠው በሁሉም ጥረትና ትብብር ቢሆንም በተለይም የባለሙያዎች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም መሰረት የቡና ምርት ዝግጅትና ግብይት ሂደት የተሳለጠ እና ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን የባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻዎችን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በክልሉ ቡናን በብዛትና በጥራት በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።
በመሆኑም የቡና አምራቾችና የመፈልፈያ ኢንዱስትሪ ባለቤቶችና አርሶ አደሮች ለቡና ምርት ጥራት ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አስገንዝበዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026