🔇Unmute
ቦንጋ፣ ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቡናን በብዛትና በጥራት በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን አስታወቀ።
የክልሉ ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ለተለያዩ የዘርፉ ባለሙያዎችና የሚመለከታቸው አካላት የቡና አዘገጃጀትና ጥራት ማስጠበቅ ላይ ያተኮረ ስልጠና እየሰጠ ነው።

በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር የደረጉት የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አስራት መኩሪያ፤ በክልሉ ከቡና ልማትና ምርታማነት በተጨማሪ ለጥራት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።
የቡና ምርትና ጥራት የሚረጋገጠው በሁሉም ጥረትና ትብብር ቢሆንም በተለይም የባለሙያዎች ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም መሰረት የቡና ምርት ዝግጅትና ግብይት ሂደት የተሳለጠ እና ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን የባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻዎችን ግንዛቤ የማሳደግ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በክልሉ ቡናን በብዛትና በጥራት በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንስተው ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።
በመሆኑም የቡና አምራቾችና የመፈልፈያ ኢንዱስትሪ ባለቤቶችና አርሶ አደሮች ለቡና ምርት ጥራት ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ አስገንዝበዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025