የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የጌዴኦ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን ጣቢያ የዞኑን የልማት አቅሞችና ባህላዊ እሴቶችን ለማስተዋወቅ ተጨማሪ አቅም ነው   

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ፤ ጥቅምት 17/2018 (ኢዜአ)፡-የጌዴኦ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን ጣቢያ የዞኑን የልማት አቅሞችና ባህላዊ እሴቶች ለማስተዋወቅ ተጨማሪ አቅም መሆኑን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።

የጌዴኦ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን ጣቢያ መደበኛ ስርጭቱን ዛሬ በይፋ ጀምሯል።

በወቅቱ ‎የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) እንደገለጹት የጌዴኦ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን ጣቢያ የጌዴኦን የልማት አቅሞች ባህላዊ እሴቶችና የቱሪዝም ሀብቶች ለማስተዋወቅና አብሮነትን ለማጠናከር የጎላ ሚና አለው።


የጌዴኦ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን ጣቢያ መደበኛ ስርጭት መጀመሩ በዚህ ረገድ የራሱ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸው፣ በተለይ የጌዴኦን ባህላዊ እሴቶችና የቱሪዝም ሃብቶች በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ ድርሻቸው የጎላ ነው ብለዋል።

ጣቢያው የህዝቦችን ትስስር ከማጠናከር ባለፈ ሀገራዊና አካባቢያዊ ልማቶችን ለማፋጠንና የመረጃ ፍሰትን ለማሳለጥ ጠንክሮ መስራት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

የማህበረሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እንዲፈቱና የጋራ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል።

የጌዴኦ ማህበረሰብ ቴሌቪዥን ጣቢያ ላለፉት ዘጠኝ ወራት በሙከራ ደረጃ ቆይቶ ዛሬ መደበኛ ስርጭት መጀመሩን የገለጹት ደግሞ የጣቢያው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ በቀለ ናቸው።

የህዝብን ባህልና ቋንቋ፣ የቱሪዝም ሀብቶች እንዲሁም የልማት ውጥኖችን በማስተዋወቅ የህብረተሰቡን የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ጣቢያው ጌዴኡፋንን ጨምሮ በሦስት ቋንቋዎችና በተለያዩ ይዘቶች የ24:00 ሰዓት ስርጭት እንደሚኖረውም ገልጸዋል።

‎የጌዴኦ ቴሌቪዥን ጠቅላላ ጉባኤ ሰብሳቢ አቶ ፀጋዬ ኦብሴ በበኩላቸው ጣቢያው የህዝቦችን ትስስር በማጠናከርና ገዥ ትርክትን በመገንባት ረገድ ትልቅ ሥራ ይጠበቅበታል ብለዋል።

በተለይ የሰላም እሴቶችን በማጉላትና በህብረተሰቡ ውስጥ በማስረጽ ለህዝቦች አንድነትና የጋራ ተጠቃሚነት መትጋት እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ለቴሌቪዥን ጣቢያው መቋቋም አስተዋጾ ላበረከቱ አካላት እውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026