🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በብሔራዊ ጥቅሟ ላይ ኢ-ፍትሃዊና ኢ-ርታዊ ውሳኔ የተወሰነባት ሀገር ናት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገልጸዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዓባይ ውሃ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት በሚመለከት በሰጡት ማብራሪያ ኢትዮጵያ በብሔራዊ ጥቅሟ ላይ ኢ-ፍትሃዊና ኢ-ርታዊ ውሳኔ የተወሰነባት ሀገር ናት ብለዋል።
ዓባይን መጠቀም ተፈጥሯዊና ህጋዊ መብቷ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሃብቱን በጋራ ለመጠቀም በቂ ነው ኢትዮጵያ አሁንም ያላት አቋም ግልጽ ነው ነው ያሉት።
ግብጻዊያንም ሱዳናዊያንም ወንድሞቻችን ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለዚህ የሚያዋጣው በመነጋገርና በመተባበር በጋራ ማደግ ነው ብለዋል።
እኛ ማንንም በሚጎዳ መልኩ አናቅድም አንሰራም ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025