የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክህሎት ኢትዮጵያ መርሃ ግብር በቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ በተከናወኑ ስራዎች አስደናቂ ውጤቶች እየተገኙ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19/2018(ኢዜአ)፦ በክህሎት ኢትዮጵያ መርሃ ግብር በቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ ከወጣቶች ጋር በተከናወኑ ስራዎች አስደናቂ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን የስራና ከህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።

በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የተመረቱ የተኪ ምርት ቴክኖሎጂዎች ማስተዋወቂያ ፕሮግራም እየተካሄደ ይገኛል።


ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ችግሮችን ወደ ዕድል ለመቀየር ከሚተጉ ወጣቶች ጋር የሚከናወኑ ተግባራትን በማጠናከር ኢትዮጵያን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እየተሰራ ነው።

ባለፉት ሁለት ዓመታት በተካሔደው በክህሎት ኢትዮጵያ ፕሮግራም የቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ ስራዎች ከወጣቶች ጋር በተከናወኑ ስራዎች አስደናቂ ውጤቶች እየተገኙ ነው ብለዋል።

ችግር ፈቺና በርካታ ስራዎችን ማከናወን የሚያስችሉ አማራጮች ያሏቸው ቴክኖሎጂዎች በስፋት እየተመረቱ መሆኑን ተናግረዋል።


በመሆኑም የፈጠራ ሰራዎችን ወደ ምርት ለማስገባት የግሉ ዘርፍ በስፋት እንዲሰማራም ጠይቀዋል።

በዛሬው እለት በተካሔደው መርሃ ግብር ላይ የቀረቡት ቴክኖሎጂዎች በመደመር እሳቤ ክህሎትና እውቀትን በጋራ መምራት እንደሚቻል የሚያመላክቱ ናቸው ብለዋል።

የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በኢትዮጵያ ፈጠራን ማበረታታት ፍጥነትን ማሳደግ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ነን ሲሉም ገልጸዋል።


በኢንስቲትዩቱ ለመጀመሪያ ጊዜ አዳዲስ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች መመረታቸውንም ተናግረዋል።

ለአብነትም ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንዳክሸን ሞተር መሰራቱን ፣ የኤሌትሪክ ተሸከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ቴክኖሎጂ ፣ ስማርት የመንገድ ዳር መብራቶች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል።

በቴክኖሎጂ ማስተዋወቂያ መርሃ ግብሩ ላይ ስራዎቻቸውን ካቀረቡት መካከል በኢንስቲትዩቱ የቴክኖሎጂ ዲፓርትመንት ቴክኖሎጂ ዴስክ ሀላፊ አቶ ወጋየው ሙሉነህ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንዳክሸን ሞተር መስራቱን ገልጸው፤ ፈጠራውን ማንኛውንም ሞተር ማንቀሳቀስ የሚያስችል ለኢንዱስትሪዎች ትልቅ ጠቀሜታ ያለውና የውጭ ምንዛሬ ወጪን መቀነስ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።


በቴክኖሎጂ ፈጠራ የተሰማራው ወጣት አቤል ማሰረሻ በበኩሉ ስማርት የመንገድ ዳር መብራቶች መስራቱን ገልጾ ዘመናዊ ቴክኖሎጂው ከመብራት አገልግሎት በተጨማሪ ካሜራና ሌሎች ሴንሰሮች ያለው በመሆኑ መረጃ እንደሚሰበሰብም ጠቁሟል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025