🔇Unmute
ባሕርዳር፤ ጥቅምት 20 /2018 (ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል የተከሰተው የግሪሳ ወፍ በደረሰ ሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በአውሮፕላን የኬሚካል ርጭትና በባሕላዊ ዘዴ የመከላከል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የዕፅዋት ጥበቃ ባለሙያ አቶ አበበ አናጋው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ሰሜን ሸዋ፣ ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደርና ደቡብ ወሎ ዞኖች የተከሰተውን የግሪሳ ወፍ ለመቆጣጠር በባህላዊና በአውሮፕላን የታገዘ ጥረት እየተደረገ ነው።
የግሪሳ ወፉ በሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በአውሮፕላን የታገዘ የኬሚካል ርጭት እየተከናወነ የሚገኘውም በተለዩ 22 የግሬሳ ወፍ የማደሪያ ቦታዎች ላይ መሆኑን አስረድተዋል።
ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባባር እየተከናወነ በሚገኘው የኬሚካል ርጭት ሥራም ከ100 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የለማ የማሽላና ሌሎች ሰብሎችን ከጉዳት መታደግ መቻሉን አንስተዋል።
ለርጭት የሚያገለግለው አውሮፕላን መነሻውን በደቡብ ወሎ ዞን ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ በማድረግ ስራውን በውጤታማነት እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመው ፤ ለርጭት በማይመቹ ቦታዎች ደግሞ አርሶ አደሩ በባሕላዊ ዘዴ እንዲከላከል እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የግሪሳ ወፍ ከማደሪያ ቦታው እስከ 64 ኪሎ ሜትር በመብረር የደረሰ ሰብልን የሚያጠፋ መሆኑን ጠቁመው፤ የተጀመረውን የመከላከል ስራ በማጠናከር ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ ደጀኔ ከበደ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በዞኑ ዳዋጨፋና ጅሌ ጥሙጋ ወረዳዎች በተለዩ አምስት የማደሪያ ቦታዎች የተከሰተውን የግሬሳ ወፍ የማጥፋት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
እስካሁን በተደረገው የኬሚካል ርጭት ከግማሽ በላይ የሚሆነውን የግሪሳ ወፍ በሚያድርበት ቦታ ማጥፋት መቻሉንና ቀሪውንም በአጭር ጊዜ ለማስወገድ እየተሰራ ነው ብለዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025