🔇Unmute
ባሕርዳር፤ ጥቅምት 20 /2018 (ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል የተከሰተው የግሪሳ ወፍ በደረሰ ሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በአውሮፕላን የኬሚካል ርጭትና በባሕላዊ ዘዴ የመከላከል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የዕፅዋት ጥበቃ ባለሙያ አቶ አበበ አናጋው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ሰሜን ሸዋ፣ ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደርና ደቡብ ወሎ ዞኖች የተከሰተውን የግሪሳ ወፍ ለመቆጣጠር በባህላዊና በአውሮፕላን የታገዘ ጥረት እየተደረገ ነው።
የግሪሳ ወፉ በሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በአውሮፕላን የታገዘ የኬሚካል ርጭት እየተከናወነ የሚገኘውም በተለዩ 22 የግሬሳ ወፍ የማደሪያ ቦታዎች ላይ መሆኑን አስረድተዋል።
ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባባር እየተከናወነ በሚገኘው የኬሚካል ርጭት ሥራም ከ100 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የለማ የማሽላና ሌሎች ሰብሎችን ከጉዳት መታደግ መቻሉን አንስተዋል።
ለርጭት የሚያገለግለው አውሮፕላን መነሻውን በደቡብ ወሎ ዞን ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ በማድረግ ስራውን በውጤታማነት እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመው ፤ ለርጭት በማይመቹ ቦታዎች ደግሞ አርሶ አደሩ በባሕላዊ ዘዴ እንዲከላከል እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የግሪሳ ወፍ ከማደሪያ ቦታው እስከ 64 ኪሎ ሜትር በመብረር የደረሰ ሰብልን የሚያጠፋ መሆኑን ጠቁመው፤ የተጀመረውን የመከላከል ስራ በማጠናከር ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ ደጀኔ ከበደ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በዞኑ ዳዋጨፋና ጅሌ ጥሙጋ ወረዳዎች በተለዩ አምስት የማደሪያ ቦታዎች የተከሰተውን የግሬሳ ወፍ የማጥፋት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
እስካሁን በተደረገው የኬሚካል ርጭት ከግማሽ በላይ የሚሆነውን የግሪሳ ወፍ በሚያድርበት ቦታ ማጥፋት መቻሉንና ቀሪውንም በአጭር ጊዜ ለማስወገድ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026