🔇Unmute
ባሕርዳር፤ ጥቅምት 20 /2018 (ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል የተከሰተው የግሪሳ ወፍ በደረሰ ሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በአውሮፕላን የኬሚካል ርጭትና በባሕላዊ ዘዴ የመከላከል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የዕፅዋት ጥበቃ ባለሙያ አቶ አበበ አናጋው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ሰሜን ሸዋ፣ ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደርና ደቡብ ወሎ ዞኖች የተከሰተውን የግሪሳ ወፍ ለመቆጣጠር በባህላዊና በአውሮፕላን የታገዘ ጥረት እየተደረገ ነው።
የግሪሳ ወፉ በሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በአውሮፕላን የታገዘ የኬሚካል ርጭት እየተከናወነ የሚገኘውም በተለዩ 22 የግሬሳ ወፍ የማደሪያ ቦታዎች ላይ መሆኑን አስረድተዋል።
ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባባር እየተከናወነ በሚገኘው የኬሚካል ርጭት ሥራም ከ100 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የለማ የማሽላና ሌሎች ሰብሎችን ከጉዳት መታደግ መቻሉን አንስተዋል።
ለርጭት የሚያገለግለው አውሮፕላን መነሻውን በደቡብ ወሎ ዞን ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ በማድረግ ስራውን በውጤታማነት እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመው ፤ ለርጭት በማይመቹ ቦታዎች ደግሞ አርሶ አደሩ በባሕላዊ ዘዴ እንዲከላከል እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የግሪሳ ወፍ ከማደሪያ ቦታው እስከ 64 ኪሎ ሜትር በመብረር የደረሰ ሰብልን የሚያጠፋ መሆኑን ጠቁመው፤ የተጀመረውን የመከላከል ስራ በማጠናከር ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ ደጀኔ ከበደ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በዞኑ ዳዋጨፋና ጅሌ ጥሙጋ ወረዳዎች በተለዩ አምስት የማደሪያ ቦታዎች የተከሰተውን የግሬሳ ወፍ የማጥፋት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
እስካሁን በተደረገው የኬሚካል ርጭት ከግማሽ በላይ የሚሆነውን የግሪሳ ወፍ በሚያድርበት ቦታ ማጥፋት መቻሉንና ቀሪውንም በአጭር ጊዜ ለማስወገድ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026