የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአማራ ክልል የግሪሳ ወፍ በሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በአውሮፕላን የታገዘ የመከላከል ሥራ እየተከናወነ ነው

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕርዳር፤ ጥቅምት 20 /2018 (ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል የተከሰተው የግሪሳ ወፍ በደረሰ ሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በአውሮፕላን የኬሚካል ርጭትና በባሕላዊ ዘዴ የመከላከል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የዕፅዋት ጥበቃ ባለሙያ አቶ አበበ አናጋው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ሰሜን ሸዋ፣ ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደርና ደቡብ ወሎ ዞኖች የተከሰተውን የግሪሳ ወፍ ለመቆጣጠር በባህላዊና በአውሮፕላን የታገዘ ጥረት እየተደረገ ነው።

የግሪሳ ወፉ በሰብል ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በአውሮፕላን የታገዘ የኬሚካል ርጭት እየተከናወነ የሚገኘውም በተለዩ 22 የግሬሳ ወፍ የማደሪያ ቦታዎች ላይ መሆኑን አስረድተዋል።

ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባባር እየተከናወነ በሚገኘው የኬሚካል ርጭት ሥራም ከ100 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ የለማ የማሽላና ሌሎች ሰብሎችን ከጉዳት መታደግ መቻሉን አንስተዋል።

ለርጭት የሚያገለግለው አውሮፕላን መነሻውን በደቡብ ወሎ ዞን ኮምቦልቻ አውሮፕላን ማረፊያ በማድረግ ስራውን በውጤታማነት እያከናወነ እንደሚገኝ ጠቁመው ፤ ለርጭት በማይመቹ ቦታዎች ደግሞ አርሶ አደሩ በባሕላዊ ዘዴ እንዲከላከል እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የግሪሳ ወፍ ከማደሪያ ቦታው እስከ 64 ኪሎ ሜትር በመብረር የደረሰ ሰብልን የሚያጠፋ መሆኑን ጠቁመው፤ የተጀመረውን የመከላከል ስራ በማጠናከር ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማትና ጥበቃ ቡድን መሪ ደጀኔ ከበደ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ በዞኑ ዳዋጨፋና ጅሌ ጥሙጋ ወረዳዎች በተለዩ አምስት የማደሪያ ቦታዎች የተከሰተውን የግሬሳ ወፍ የማጥፋት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

እስካሁን በተደረገው የኬሚካል ርጭት ከግማሽ በላይ የሚሆነውን የግሪሳ ወፍ በሚያድርበት ቦታ ማጥፋት መቻሉንና ቀሪውንም በአጭር ጊዜ ለማስወገድ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026