የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ አዲሱን የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለማሰራጨት ዝግጅት እየተደረገ ነው - ቢሮው

Nov 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚዛን አማን፤ጥቅምት 22/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል አዲሱን የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለማሰራጨት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ምክትል እና የትራንስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዘመዴ አንዳርጌ ለኢዜአ እንደገለጹት አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ በቴክኖሎጂ የተደገፈና የተለያዩ መረጃዎችን አካቶ የተዘጋጀ ነው።

ይህም ነባሩ ሰሌዳ ለሕገወጥ ተግባር ያለውን ተጋላጭነት ከማስቀረት ባለፈ ክልላዊ መለያ ያለውን ታርጋ ስለሚያስቀር ለሀገራዊ አንድነት መጠናከር አስተዋጾ እንደሚኖረው ገልጸዋል።

የተሽከርካሪ መረጃዎችን በዲጂታል አሰራር ለመለየት የሚያስችልና ከዓለም አቀፍ ስምምነቶች ጋር ተዛማጅ እንዲሆን ተደርጎ የተዘጋጀ በመሆኑ ለአሠራርና ለቁጥጥር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር አክለዋል።

አዲሱን ሰሌዳ በክልሉ ውስጥ ላሉ ከ34 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች ለማሰራጨት አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አቶ ዘመዴ ተናግረዋል።

እስካሁንም አስፈላጊ መረጃዎችን ለይቶ ለትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የማሳወቅና መሰል ዝግጅቶች መደረጋቸውን ጠቁመው፣ ለዚሁ ተግባር 20 ሚሊዮን ብር በጀት መመደቡንም አመልክተዋል።

አስተያየታቸውን ከሰጡ አሽከርካሪዎች መካከል አቶ ሺመልስ ታደሰ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ እንደሀገር ወጥ በሆነ መንገድ መዘጋጀቱ በነጻነት ተንቀሳቅሶ ለመስራት ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ተናግሯል።

"ከክልል ወደ ክልል ተዘዋውሮ ለመሥራት በሚደረግ እንቅስቃሴ በተለያዩ ምክንያቶች ሲገጥመን የነበረን እንግልት ያስቀራል" ሲልም ተስፋውን ገልጿል።

ሰሌዳው እንደሀገር ወጥ በሆነ መንገድ መዘጋጀቱ የብዙዎች ፍላጎት እንደነበር አስታውሶ ይህም ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከርና በሁሉም ክልሎች በነጻነት ለመንቀሳቀስ ያግዛል ብሏል።

በትራፊክ አሰራር ላይ ሲስተዋል የነበረውን ብልሹ አሠራር ያስቀራል የሚል እምነት እንዳለው የተናገረው ደግሞ ሌላው አሽከርካሪ አዝማች አደመ ነው።

መንግስት የተሽከርካሪ ሰሌዳን ሀገራዊ አድርጎ በአዲስ መልክ የማዘጋጀቱ ጥረት የሚበረታታና የሚደገፍ መሆኑን ተናግሯል።

የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያሳየው በሀገር አቀፍ ደረጃ በሥራ ላይ ያለውን ሰሌዳ በተያዘው ዓመት ሙሉ በሙሉ በአዲስ የመተካት ሥራ ይከናወናል።

ነባሩ ሰሌዳ ከዘርፉ እድገትና ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ጋር አብሮ የማይሄድ በመሆኑ በአዲስ ሰሌዳ መተካት ማስፈለጉም ቀደምሲል መገለጹ የሚታወስ ነው።

አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ በቴክኖሎጂ በታገዘ አሰራር የሚመራ በመሆኑ ለቁጥጥር ስርዓትም አመቺ እንደሆነም ተመላክቷል።

ሰሌዳው ስለተሽከርካሪው ሙሉ መረጃ የሚሰጡና ተቆጣጣሪ አካላት በቴክኖሎጂ የሚለዩዋቸው ሚስጥራዊ መረጃዎችን ያካተተ እንደሆነም የሚኒስቴሩ መረጃ ያሳያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025