የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በሐረሪ ክልል በዘንድሮ ዓመት በበጋ መስኖ 4 ሺህ 851 ሄክታር መሬት ይለማል

Nov 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐረር ፤ጥቅምት 23/2018(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በዘንድሮ የበጋ መስኖ 4 ሺህ 851 ሄክታር መሬት እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ ገለጸ፡፡

የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ነስረዲን አህመድ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ በዘንድሮ የበጋ ወቅት መስኖ እርሻ ያሉትን የውሃ አማራጮች በሙሉ በመጠቀም 4 ሺህ 851 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡

በመስኖው የሚለማውም ሽንኩርት፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመን፣ ቃሪያ፣ ካሮትና ሌሎች የአትክልትና የሰብል ዓይነት መሆናቸውን ተናግረዋል።


በሁለት ዙር በመስኖ ከሚለማው መሬትም በድምሩ ከ1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ዘንድሮ በመስኖ የሚለማው መሬት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፃር በ402 ሄክታር መሬት ብልጫ እንዳለውም አቶ ነስሩ ተናግረዋል።

ለመስኖ ልማቱ ምርጥ ዘርና ሌሎች የምርት ማሳደጊያ ግብዓት በቢሮውና በወረዳዎች መሟላቱን ገልጸዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ለመስኖ ልማቱ የሚያገለግል ተጨማሪ 200 የውሃ መሳቢያ ሞተሮችና ዲናሞ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱንም ተናግረዋል።


በየደረጃው ለሚገኙ የግብርና ባለሙያዎችና የልማት ጣቢያ ሰራተኞች አስፈላጊው የቴክኒክና የሙያ ስልጠና መሰጠቱንም ገልጸዋል።

በክልሉ ባለፈው ተመሳሳይ ዓመት 4ሺህ 449 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ መልማቱን ጠቅሰዋል።

የመስኖ ልማቱ በተለይም የአትክልትና ፍራፍሬ ምርት አርሶ አደሩንና የከተማ ነዋሪውን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ መረጋጋት እየፈጠረ እንደሚገኝና ህብረተሰቡም ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻሉም አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026