🔇Unmute
ሐረር ፤ጥቅምት 23/2018(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በዘንድሮ የበጋ መስኖ 4 ሺህ 851 ሄክታር መሬት እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ ገለጸ፡፡
የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ነስረዲን አህመድ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ በዘንድሮ የበጋ ወቅት መስኖ እርሻ ያሉትን የውሃ አማራጮች በሙሉ በመጠቀም 4 ሺህ 851 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡
በመስኖው የሚለማውም ሽንኩርት፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመን፣ ቃሪያ፣ ካሮትና ሌሎች የአትክልትና የሰብል ዓይነት መሆናቸውን ተናግረዋል።

በሁለት ዙር በመስኖ ከሚለማው መሬትም በድምሩ ከ1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ዘንድሮ በመስኖ የሚለማው መሬት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፃር በ402 ሄክታር መሬት ብልጫ እንዳለውም አቶ ነስሩ ተናግረዋል።
ለመስኖ ልማቱ ምርጥ ዘርና ሌሎች የምርት ማሳደጊያ ግብዓት በቢሮውና በወረዳዎች መሟላቱን ገልጸዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ለመስኖ ልማቱ የሚያገለግል ተጨማሪ 200 የውሃ መሳቢያ ሞተሮችና ዲናሞ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱንም ተናግረዋል።

በየደረጃው ለሚገኙ የግብርና ባለሙያዎችና የልማት ጣቢያ ሰራተኞች አስፈላጊው የቴክኒክና የሙያ ስልጠና መሰጠቱንም ገልጸዋል።
በክልሉ ባለፈው ተመሳሳይ ዓመት 4ሺህ 449 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ መልማቱን ጠቅሰዋል።
የመስኖ ልማቱ በተለይም የአትክልትና ፍራፍሬ ምርት አርሶ አደሩንና የከተማ ነዋሪውን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ መረጋጋት እየፈጠረ እንደሚገኝና ህብረተሰቡም ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻሉም አመላክተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025