🔇Unmute
ሐረር ፤ጥቅምት 23/2018(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል በዘንድሮ የበጋ መስኖ 4 ሺህ 851 ሄክታር መሬት እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ ገለጸ፡፡
የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ነስረዲን አህመድ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ በዘንድሮ የበጋ ወቅት መስኖ እርሻ ያሉትን የውሃ አማራጮች በሙሉ በመጠቀም 4 ሺህ 851 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡
በመስኖው የሚለማውም ሽንኩርት፣ ቲማቲም፣ ጥቅል ጎመን፣ ቃሪያ፣ ካሮትና ሌሎች የአትክልትና የሰብል ዓይነት መሆናቸውን ተናግረዋል።

በሁለት ዙር በመስኖ ከሚለማው መሬትም በድምሩ ከ1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ዘንድሮ በመስኖ የሚለማው መሬት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፃር በ402 ሄክታር መሬት ብልጫ እንዳለውም አቶ ነስሩ ተናግረዋል።
ለመስኖ ልማቱ ምርጥ ዘርና ሌሎች የምርት ማሳደጊያ ግብዓት በቢሮውና በወረዳዎች መሟላቱን ገልጸዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ለመስኖ ልማቱ የሚያገለግል ተጨማሪ 200 የውሃ መሳቢያ ሞተሮችና ዲናሞ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱንም ተናግረዋል።

በየደረጃው ለሚገኙ የግብርና ባለሙያዎችና የልማት ጣቢያ ሰራተኞች አስፈላጊው የቴክኒክና የሙያ ስልጠና መሰጠቱንም ገልጸዋል።
በክልሉ ባለፈው ተመሳሳይ ዓመት 4ሺህ 449 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ መልማቱን ጠቅሰዋል።
የመስኖ ልማቱ በተለይም የአትክልትና ፍራፍሬ ምርት አርሶ አደሩንና የከተማ ነዋሪውን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ መረጋጋት እየፈጠረ እንደሚገኝና ህብረተሰቡም ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻሉም አመላክተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025