የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በደብረ ማርቆስ ከተማ  ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን  ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ 

Nov 7, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ማርቆስ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፡ - በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ሶሰት ወራት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ሃላፊ ተመስገን ተድላ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የከተማ አስተዳደሩ ለባለሃብቱ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት ከታቀደው ውስጥ በመጀመሪያዎቹ ሶሰት ወራት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊየን ብር በላይ ላስመዘገቡ 33 ባለሃብቶች ፈቃድ መሰጠቱን አስታውቀዋል።

ባለሀብቶቹ ለመሰማራት ፈቃድ ከወሰዱባቸው ዘርፎች መካከል የዘይት፣ ሚስማር ፣የጨርቃጨርቅና ዱቄት ፋብሪካ እንዲሁም ሆቴል እና ቱሪዝም እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።

ፈቃድ ከተሰጣቸው ውስጥ ለ20ዎቹ ባለሃብቶች ከ12 ሄክታር በላይ መሬት የተሰጣቸው ሲሆን፤ ቀሪዎቹንም ባቀረቡት ፕሮጀክት መሰረት ለማስተናገድ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቀጣይም ተጨማሪ አዳዲስ ባለሃብቶችን በመሳብና ፈቃድ ለወሰዱት ደግሞ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ፈጥነው ወደ ስራ እንዲገቡ የመደገፍ ተግባር እንደሚከናወን ተናግረዋል።

ፈቃድ የተሰጣቸው ባለሃብቶች ወደ ስራ ሲገቡም ከ3 ሺህ 600 በላይ ለሚሆኑ ስራ ፈላጊዎች የስራ እድል መፍጠር የሚችሉ ናቸው ብለዋል።

ፈቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ28 ባለሃብቶችና በካፒታል ደግሞ ከአንድ ነጥብ ስምንት ቢሊየን ብር ብልጫ እንዳለው ተመልክቷል።

ብልጫ ያለው ውጤት ማስመዝገብ የተቻለው ከቀድሞ በተሻለ በከተማውና አካባቢ በተፈጠር ምቹ ሁኔታ ብዛት ያላቸው ባለሀብቶችን ባሉ የኢንቨሰትመነት አማራጮች ለመሳተፍ በማሰባቸው እንደሆነ አስረድተዋል።

በሌላ በኩል የኢንቨስትመንት ቦታ ለረጅም ጊዜ አጥረው ያስቀመጡ 52 ባለሃብቶችን ውል በማቋረጥ መሬቱን ለሚያለሙ ባለሃብቶች መመቻቸቱን ተናግረዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ባዘጋጀው የኢንዱስትሪ ፓርክ ከሚገኙት 168 ፋብሪካዎች ውስጥ 36ቱ ወደ ማምረት የተሸጋገሩ መሆናቸው ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026