🔇Unmute
ደብረ ማርቆስ ፤ ጥቅምት 27/2018(ኢዜአ)፡ - በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ሶሰት ወራት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን የከተማ አስተዳደሩ ኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ሃላፊ ተመስገን ተድላ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የከተማ አስተዳደሩ ለባለሃብቱ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት ከታቀደው ውስጥ በመጀመሪያዎቹ ሶሰት ወራት ከሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊየን ብር በላይ ላስመዘገቡ 33 ባለሃብቶች ፈቃድ መሰጠቱን አስታውቀዋል።
ባለሀብቶቹ ለመሰማራት ፈቃድ ከወሰዱባቸው ዘርፎች መካከል የዘይት፣ ሚስማር ፣የጨርቃጨርቅና ዱቄት ፋብሪካ እንዲሁም ሆቴል እና ቱሪዝም እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል።
ፈቃድ ከተሰጣቸው ውስጥ ለ20ዎቹ ባለሃብቶች ከ12 ሄክታር በላይ መሬት የተሰጣቸው ሲሆን፤ ቀሪዎቹንም ባቀረቡት ፕሮጀክት መሰረት ለማስተናገድ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በቀጣይም ተጨማሪ አዳዲስ ባለሃብቶችን በመሳብና ፈቃድ ለወሰዱት ደግሞ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ፈጥነው ወደ ስራ እንዲገቡ የመደገፍ ተግባር እንደሚከናወን ተናግረዋል።
ፈቃድ የተሰጣቸው ባለሃብቶች ወደ ስራ ሲገቡም ከ3 ሺህ 600 በላይ ለሚሆኑ ስራ ፈላጊዎች የስራ እድል መፍጠር የሚችሉ ናቸው ብለዋል።
ፈቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ28 ባለሃብቶችና በካፒታል ደግሞ ከአንድ ነጥብ ስምንት ቢሊየን ብር ብልጫ እንዳለው ተመልክቷል።
ብልጫ ያለው ውጤት ማስመዝገብ የተቻለው ከቀድሞ በተሻለ በከተማውና አካባቢ በተፈጠር ምቹ ሁኔታ ብዛት ያላቸው ባለሀብቶችን ባሉ የኢንቨሰትመነት አማራጮች ለመሳተፍ በማሰባቸው እንደሆነ አስረድተዋል።
በሌላ በኩል የኢንቨስትመንት ቦታ ለረጅም ጊዜ አጥረው ያስቀመጡ 52 ባለሃብቶችን ውል በማቋረጥ መሬቱን ለሚያለሙ ባለሃብቶች መመቻቸቱን ተናግረዋል።
የከተማ አስተዳደሩ ባዘጋጀው የኢንዱስትሪ ፓርክ ከሚገኙት 168 ፋብሪካዎች ውስጥ 36ቱ ወደ ማምረት የተሸጋገሩ መሆናቸው ተመልክቷል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026