የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በቁርጠኝነት ከተሰራ ከተማ እና ሀገርን መገንባት እንደሚቻል አዲስ አበባ ማሳያ ናት - የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት 

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 29/2018 (ኢዜአ)፦በቁርጠኝነት ከተሰራ ከተማ እና ሀገርን መገንባት እንደሚቻል አዲስ አበባ ማሳያ ናት ሲሉ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ገለጹ።

የአዲስ አበባ ከተማ ስኬት ለሌሎች የሀገሪቷ አካባቢዎች አርአያ እንደሚሆንም አመራር አባላቱ ገልጸዋል።

የፓርቲው ከፍተኛ አመራር አባላት በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የኮሪደር፣ የወንዝ ዳር ልማት፣ የቤት ልማት እና አቅርቦት ስራዎችን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ መስጠፌ መሀመድ፤ በጉብኝቱ አዲስ አበባ የኢትዮጵያን ገጽታ ከፍ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎችን እያካሄደች መሆኗን ተመልክተናል ብለዋል።


በተለይም የኮንፍረንስ ቱሪዝም ማዕከልነቷን የሚያጸኑ መሰረተ ልማት ግንባታዎችን አይተናል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በአመራሩ ቁርጠኝነት ሀገር መለወጥ የሚያስችል መልካም እድል መኖሩን ያመላከተ ነው ብለዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው፤ በኦሮሚያ ክልልም ሆነ በአዲስ አበባ ያየናቸው የልማት ውጤቶች ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና ማማ ለማድረስ በትክክለኛው መስመር ላይ መሆናችንን አመላካች ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያን ትልሞች ከዳር በማድረስ ተጨማሪ ስኬቶችን ለማስመዝገብ ዝግጁ ነን ሲሉም ገልጸዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ መነቴ ሙንዲኖ በበኩላቸው፤ የአዲስ አበባ የልማት ስኬት ለሌሎች ከተሞችም ከፍተኛ ልምድ እንደሚሆን ተናግረዋል።


ልማትን ቀጣይነት ባለው መልኩ እያረጋገጡ ለመሄድ ተግባራዊ እርምጃዎችን በላቀ ደረጃ የምንወስድበት ጊዜ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025