የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎችን በማዳቀል ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ ነው

Nov 20, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 10/2018 (ኢዜአ)፡-የወተትና ስጋ ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎችን በማዳቀል ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ የወተትና ሥጋ ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎችን የማዳቀል ሥራ እየተከናወነ ነው፡፡

በዚህም በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሶስት ወራት 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ላሞችን ለማዳቀል ዕቅድ ተይዞ 1 ነጥብ 1 ሚሊየን ማሳካት መቻሉን ገልጸዋል፡፡

በተለይም በፈሳሽ ናይትሮጅን አማካኝነት የወተትና ሥጋ ምርታማነትን ማሳደግ የሚችል የተሻሻሉ ዝርያዎች እየተዳቀሉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በኢትዮጵያ ከአራት ዓመት በፊት በዓመት 500 ሺህ እንስሳት ይዳቀሉ እንደነበረ አስታውሰው፤ በዚህ ዓመት 5 ሚሊየን የተሻሻለ ዝርያ ያላቸው ላሞችን ለማዳቀል መታቀዱን ገልጸዋል፡፡

በወተትና ሥጋ ምርታማነት ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን በማነሳት፤ የተሻሻሉ የእንስሳት ዝርያዎች የምግብ ሥርዓቱን ለማሳለጥ ወሳኝ በመሆናቸው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡


ከዚህም ባሻገር ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የጎላ አበርክቶ እንዳለው ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብርን ካስጀመሩ በኋላ በሀገር አቀፍ ደረጃ እያንዳንዳቸው በሰዓት 30 ሊትር ፈሳሽ ናይትሮጅን የማምረቻ አቅም ያላቸው ማሽነሪዎች በተለያዩ ከተሞች ተተክለዋል ብለዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በግ፣ ፍየልና ሌሎች እንስሳትን ለማዳቀል የሚያገለግሉና በሰዓት 50 ሊትር ፈሳሽ ናይትሮጅን ማምረት የሚችሉ ማሽነሪዎች በግዥ ሂደት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡


ከፈሳሽ ናይትሮጂን በተጨማሪ በኮርማ አባል ዘር የማዳቀል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ የበግ፣ ፍየልና ሌሎች እንስሳትን ማዳቃል የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026