የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአማራ ክልል ያለውን የተፈጥሮ ጸጋ እና ሀብት አልምቶ በመጠቀም ምርታማነትን የማላቅ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Jul 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደሴ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ያለውን የተፈጥሮ ጸጋ እና ሀብት አልምቶ በመጠቀም ምርታማነትን የማላቅ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።

ቢሮው ከክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር "ዘመናዊ ግብርና ለሁለንተናዊ ልዕልና" በሚል መሪ ሐሳብ የምክክር መድረክ በደሴ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ የክልሉ ግብርና ቢሮ ደረጀ ማንደፍሮ እንደገለጹት፤ ክልሉ ለሰብል ልማት፣ ለእንስሳት እርባታና ለሌሎችም የግብርና ሥራዎች ምቹና ተስማሚ ነው።

ይህን የተፈጥሮ ጸጋና ሀብት አልምቶ ለመጠቀም የአሻጋሪ ዕድገትና የዘላቂ ልማት ፍኖተ ካርታ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ መገባቱን ገልጸዋል።


ፍኖተ ካርታውን ወደ መሬት በማውረድ የሚጠበቀውን ውጤት ለማስመዝገብ ለዘርፉ አመራር፣ ባለሙያና ባለድርሻ አካላት በየደረጃው ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

የምክክር መድረኩም የጋራ አመለካከትና ተልዕኮ በመያዝ በሁሉም አካባቢዎች የላቀ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።

በዚህም በሰብል ልማት፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ በእንስሳት እርባታ፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎችም የተገኘውን አበረታች ውጤት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል።

እስካሁን የተመዘገበውን ውጤት በመገምገም ክፍተቶችን ለማረም፣ ዘመናዊ የግብርና ሽግግሩን ለማፋጠን፣ የመስኖ ልማትን ለማጠናከርና ተቋማዊና ሙያዊ ኃላፊነትን በአግባቡ ለመወጣት የምክክር መድረኩ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።

አርሶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅና ቴክኖሎጂን በመጠቀም በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለገበያ የሚተርፍ ምርት እንዲያመርት የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።

አርሶ አደሩ ከኋላ ቀር አሠራር ወደ ዘመናዊ ግብርና መሸጋገር እንዲችል ተገቢው ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑንም አክለዋል።

ለሁለት ቀናት በሚካሄደው በዚህ የምክክር መድረክ ላይ ከክልል ጀምሮ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፣ የዘርፉ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026