🔇Unmute
ደሴ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ያለውን የተፈጥሮ ጸጋ እና ሀብት አልምቶ በመጠቀም ምርታማነትን የማላቅ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።
ቢሮው ከክልሉ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር "ዘመናዊ ግብርና ለሁለንተናዊ ልዕልና" በሚል መሪ ሐሳብ የምክክር መድረክ በደሴ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ የክልሉ ግብርና ቢሮ ደረጀ ማንደፍሮ እንደገለጹት፤ ክልሉ ለሰብል ልማት፣ ለእንስሳት እርባታና ለሌሎችም የግብርና ሥራዎች ምቹና ተስማሚ ነው።
ይህን የተፈጥሮ ጸጋና ሀብት አልምቶ ለመጠቀም የአሻጋሪ ዕድገትና የዘላቂ ልማት ፍኖተ ካርታ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ መገባቱን ገልጸዋል።

ፍኖተ ካርታውን ወደ መሬት በማውረድ የሚጠበቀውን ውጤት ለማስመዝገብ ለዘርፉ አመራር፣ ባለሙያና ባለድርሻ አካላት በየደረጃው ሥልጠና እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።
የምክክር መድረኩም የጋራ አመለካከትና ተልዕኮ በመያዝ በሁሉም አካባቢዎች የላቀ አፈጻጸም ለማስመዝገብ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።
በዚህም በሰብል ልማት፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ በእንስሳት እርባታ፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎችም የተገኘውን አበረታች ውጤት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል።
እስካሁን የተመዘገበውን ውጤት በመገምገም ክፍተቶችን ለማረም፣ ዘመናዊ የግብርና ሽግግሩን ለማፋጠን፣ የመስኖ ልማትን ለማጠናከርና ተቋማዊና ሙያዊ ኃላፊነትን በአግባቡ ለመወጣት የምክክር መድረኩ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
አርሶ አደሩን ከዝናብ ጥገኝነት በማላቀቅና ቴክኖሎጂን በመጠቀም በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለገበያ የሚተርፍ ምርት እንዲያመርት የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
አርሶ አደሩ ከኋላ ቀር አሠራር ወደ ዘመናዊ ግብርና መሸጋገር እንዲችል ተገቢው ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑንም አክለዋል።
ለሁለት ቀናት በሚካሄደው በዚህ የምክክር መድረክ ላይ ከክልል ጀምሮ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች፣ የዘርፉ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...
Jul 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...
Jul 3, 2026
አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...
Jun 29, 2026
ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...
Jun 25, 2026