የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የአርሶ አደሮችን ገቢ ለሚያሳድጉና ለወጪ ንግድ የሚውሉ ምርቶችን በስፋት ለማምረት ትኩረት ተደርጓል

Jul 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የአርሶ አደሮችን ገቢ ለሚያሳድጉና ለወጪ ንግድ የሚውሉ ምርቶችን በስፋት የማምረት ስራ ትኩረት ማግኘቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ ገለጹ።

በክልሉ ምስራቅ ሸዋ ዞን ቦሰት ወረዳ ቦሎቄን በኩታ ገጠም የመዝራት ሥራ የክልሉ፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች በተገኙበት ተጀምሯል።


በዚሁ ወቅት የቢሮ ኃላፊው ኃይሉ አዱኛ በክልሉ የግብርና ምርታማነትን በእጥፍ ከመጨመር ጎን ለጎን፣ የአርሶ አደሮችን ገቢ ለማሳደግ በወጪ ንግድ ምርቶች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው ብለዋል።

ዛሬ በዞኑ ቦሰት ወረዳ የዶንጎሬ ጪዮስ ቀበሌ የተጀመረው ቦሎቄን በኩታ ገጠም የመዝራት ሥራ ለዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው መሰል መልካም ተሞክሮዎች እንዲሰፉ ይደረጋል ነው ያሉት።

በተለይም የክልሉ አርሶ አደሮች ከግብርና ሥራ የሚያገኙትን ገቢ የበለጠ የሚያሳድጉ የቅባት እህሎችን በኩታ ገጠም እንዲያለሙ በትኩረት እንደሚሠራም አስረድተዋል።


የምስራቅ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አባቡ ዋቆ በበኩላቸው፣ በዞኑ ባለፈው ዓመት 90 ሺህ ሄክታር ገደማ መሬት ላይ የቅባት እህሎች መዘራታቸውን አስታውሰው፣ ዘንድሮ ይህንን ወደ 130 ሺህ ሄክታር ለማሳደግ መታቀዱን ተናግረዋል።

የተጀመረውን ሥራ የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የግብርና ግብዓቶች በወቅቱ ለአርሶ አደሩ እንዲደርሱ መደረጉን ገልጸዋል።


በቦሰት ወረዳ ለመኸር እርሻ ከተዘጋጀው 64 ሺህ ሄክታር መሬት ውስጥ 58 ሺህ ሄክታሩ በኩታ ገጠም የሚለማ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የወረዳው አስተዳዳሪ ጉተማ ቢፍቱ ናቸው።

በወረዳው በኩታ ገጠም ከሚለማው የቦሎቄ ሰብልም በሄክታር እስከ 30 ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026