🔇Unmute
አዳማ፤ ሰኔ 29/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የአርሶ አደሮችን ገቢ ለሚያሳድጉና ለወጪ ንግድ የሚውሉ ምርቶችን በስፋት የማምረት ስራ ትኩረት ማግኘቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ ገለጹ።
በክልሉ ምስራቅ ሸዋ ዞን ቦሰት ወረዳ ቦሎቄን በኩታ ገጠም የመዝራት ሥራ የክልሉ፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች በተገኙበት ተጀምሯል።

በዚሁ ወቅት የቢሮ ኃላፊው ኃይሉ አዱኛ በክልሉ የግብርና ምርታማነትን በእጥፍ ከመጨመር ጎን ለጎን፣ የአርሶ አደሮችን ገቢ ለማሳደግ በወጪ ንግድ ምርቶች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው ብለዋል።
ዛሬ በዞኑ ቦሰት ወረዳ የዶንጎሬ ጪዮስ ቀበሌ የተጀመረው ቦሎቄን በኩታ ገጠም የመዝራት ሥራ ለዚህ አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቅሰው መሰል መልካም ተሞክሮዎች እንዲሰፉ ይደረጋል ነው ያሉት።
በተለይም የክልሉ አርሶ አደሮች ከግብርና ሥራ የሚያገኙትን ገቢ የበለጠ የሚያሳድጉ የቅባት እህሎችን በኩታ ገጠም እንዲያለሙ በትኩረት እንደሚሠራም አስረድተዋል።

የምስራቅ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አባቡ ዋቆ በበኩላቸው፣ በዞኑ ባለፈው ዓመት 90 ሺህ ሄክታር ገደማ መሬት ላይ የቅባት እህሎች መዘራታቸውን አስታውሰው፣ ዘንድሮ ይህንን ወደ 130 ሺህ ሄክታር ለማሳደግ መታቀዱን ተናግረዋል።
የተጀመረውን ሥራ የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የግብርና ግብዓቶች በወቅቱ ለአርሶ አደሩ እንዲደርሱ መደረጉን ገልጸዋል።

በቦሰት ወረዳ ለመኸር እርሻ ከተዘጋጀው 64 ሺህ ሄክታር መሬት ውስጥ 58 ሺህ ሄክታሩ በኩታ ገጠም የሚለማ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የወረዳው አስተዳዳሪ ጉተማ ቢፍቱ ናቸው።
በወረዳው በኩታ ገጠም ከሚለማው የቦሎቄ ሰብልም በሄክታር እስከ 30 ኩንታል ምርት ለማግኘት መታቀዱን ተናግረዋል።
ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...
Jul 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...
Jul 3, 2026
አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...
Jun 29, 2026
ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...
Jun 25, 2026