የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ በመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በቅንጅት የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

Jul 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ቦንጋ፤ ሰኔ29/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በቅንጅት የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ።

በክልሉ በመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል የማሳ፣ የግብዓትና መሰል ዝግጅቶች መደረጋቸውም ተመላክቷል።

የክልሉን ያለፈው ዓመት የመኸር አርሻ አፈጻጸም ለመገምገምና የዘንድሮውን የመኸር ግብርና በማስመልከት የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል።


የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በመድረኩ እንደገለጹት፣ በክልሉ የመኸር እርሻን ስኬታማ ለማድረግ የሚደረጉ ጥረቶች በተቀናጀ መልኩ ተጠናክረው ይቀጥላሉ።

በየደረጃው ለአርሶ አደሩ የሚደረገውን ድጋፍና ክትትል በማጠናከርና የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሻሻል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ለመኸር እርሻው ምርጥ ዘር እና የአፈር ማዳበሪያ በበቂ ሁኔታ መቅረቡን አቶ ማስረሻ ጠቁመው፣ በልማቱ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ድጋፍና ክትትሉ መጠናከር እንዳለበት አስገንዝበዋል።

እንደኃላፊው ገለጻ በክልሉ በመኸር ወቅት ከ463ሺህ ሄክታር ማሳ በአዝርት፣ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት የሚሸፈን ሲሆን ከልማቱም ከ20 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል።

በክልሉ የተለያዩ ዞኖች የግብርና መምሪያ ሃላፊዎችም በመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ለግብርና ቴክኖሎጂ ፣ለማሳ ዝግጅትና ለግብአት አቅርቦትና አጠቃቀም ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።


ከሀላፊዎቹ መካከል የዳውሮ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ሕብረት ሥራ መምሪያ ሀላፊ ረዳት ፕሮፌሰር በተላ በየነ እንደገለጹት፣ የመኸር እርሻን ስኬታማ ለማድረግ የአርሶ አደሩን የግብርና ግብአት አጠቃቀም ከማሻሻል በተጨማሪ የድጋፍና ክትትል ሥራው ይጠናከራል።

በዞኑ ከ90ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመኸሩ ለማልማት መታቀዱን ገልጸው፣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ማዳበሪያና ምርጥ ዘርን ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ገልጸዋል።

ከማሳ ዝግጅት ጀምሮ በግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ የድጋፍና ክትትል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስታውቀዋል።

ሜካናይዜሽን እና ኩታ ገጠም እርሻን በማስፋት የተሻለ ምርት ለመሰብሰብ እንደሚሰራ የተናገሩት ደግሞ የካፋ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ሕብረት ሥራ መምሪያ ሀላፊ አቶ ገረመው ገብሬ ናቸው።


በዞኑ 139 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት 3 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸው፣ የታቀደውን ለማሳካት ግብአት ከማቅረብ ባለፈ የባለሙያዎች ድጋፍና እገዛ ይጠናከራል ብለዋል።


የሸካ ዞን ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ሕብረት ሥራ መምሪያ ሀላፊ አቶ አይምሮ ደሳለኝ በበኩላቸው፣ በዞኑ ዘንድሮ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የማሳ፣ የግብዓትና ሌሎች አስፈላጊ ዝግጅቶች መደረጋቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026