የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከለውጡ በፊት ከነበረው መንገደኞችን የማጓጓዝ አቅም በለውጡ ዓመታት በሶስት እጥፍ አሳድጓል

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከለውጡ በፊት ከነበረው መንገደኞችን የማጓጓዝ አቅም በለውጡ ዓመታት በሶስት እጥፍ ማሳደጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአገልግሎት ዘርፍ በሰጡት ማብራሪያ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአገልግሎቱ አድማሱ እየሰፋ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከለውጡ በፊት ከነበረው መንገደኞችን የማጓጓዝ አቅም በለውጡ ዓመታት በሶስት እጥፍ ማሳደግ እንደቻለ ተናግረዋል።

ለማሳያም የዚህ ዓመቱን ያነሱ ሲሆን በ2018 ዓ.ም አየር መንገዱ አጠቃላይ 21 ሚሊየን የውጭና የሀገር ውስጥ መንገደኞችን ማጓጓዙን ገልጸዋል።

ከላይ ከተጠቀሰው ቁጥር ውስጥ 17 ሚሊየን የሚሆኑት የውጭ ሀገራት ተጓዦችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ማጓጓዝ እንደቻለ አብራርተዋል።

አየር መንገዱ በሰጠው አገልግሎትም ለኢትዮጵያ ሃብት እንድታገኝ አቅም መፍጠሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026