🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከለውጡ በፊት ከነበረው መንገደኞችን የማጓጓዝ አቅም በለውጡ ዓመታት በሶስት እጥፍ ማሳደጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአገልግሎት ዘርፍ በሰጡት ማብራሪያ፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአገልግሎቱ አድማሱ እየሰፋ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከለውጡ በፊት ከነበረው መንገደኞችን የማጓጓዝ አቅም በለውጡ ዓመታት በሶስት እጥፍ ማሳደግ እንደቻለ ተናግረዋል።
ለማሳያም የዚህ ዓመቱን ያነሱ ሲሆን በ2018 ዓ.ም አየር መንገዱ አጠቃላይ 21 ሚሊየን የውጭና የሀገር ውስጥ መንገደኞችን ማጓጓዙን ገልጸዋል።
ከላይ ከተጠቀሰው ቁጥር ውስጥ 17 ሚሊየን የሚሆኑት የውጭ ሀገራት ተጓዦችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ማጓጓዝ እንደቻለ አብራርተዋል።
አየር መንገዱ በሰጠው አገልግሎትም ለኢትዮጵያ ሃብት እንድታገኝ አቅም መፍጠሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው አንስተዋል።
ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...
Jul 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...
Jul 3, 2026
አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...
Jun 29, 2026
ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...
Jun 25, 2026