🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን የምርታማነት አቅም ይበልጥ በማሳደግ እና የተለያዩ እርምጃዎችን በመውሰድ የኑሮ ውድነት ጫናን ለመቀነስ በትኩረት እንደሚሰራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ የ2018 በጀት ዓመት የመንግሥት አፈጻጸምን በተመለከተ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማብራሪያቸው እንደገለጹት፤ መንግሥት የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት በርካታ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል።
ከተወሰዱ ቀዳሚ እርምጃዎች መካከል የሸማቾችን አማራጭ ማሳደግ አንዱ ሲሆን፣ በዚህም የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን ተደራሽነት ከ2000 በላይ ማድረስ መቻሉን አስታውቀዋል።
የኑሮ ውድነቱን ጫና ለማቅለል መንግሥት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ድጎማ እያደረገ ይገኛል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በተለይም በነዳጅ ዘርፍ ላይ ይደረግ የነበረው ድጎማ በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን አስታውቀዋል።
ቀድሞ የነበረው የነዳጅ ድጎማ በወር 16 ቢሊዮን ብር እንደነበር ጠቁመው፤ በአሁኑ ወቅት 20 ቢሊዮን ብር በመጨመር የድጎማ መጠኑን በወር ወደ 36 ቢሊዮን ብር ማሳደግ መቻሉን ጠቁመዋል።
ይህ የሕዝቡን የመግዛት አቅም ለማሳደግ የተመደበ ትልቅ ሀገራዊ አቅም መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች በየደረጃውና በልፋታቸው ልክ ተጠቃሚ ማድረግ አለበትም ነው ያሉት።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026