የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአፍሪካ ቀዳሚና ተወዳዳሪ የሆነ የጥራት ማረጋገጫ ተቋም ተገንብቷል

Jul 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 1/2018(ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ቀዳሚና ተወዳዳሪ የሆነ የጥራት ማረጋገጫ ተቋም መገንባቱን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መዓዛ አበራ ገለጹ፡፡

ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ ከ36 ሺህ በላይ የምርት ጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶችን መስጠት መቻሉንም ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መዓዛ አበራ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ድርጅቱ በተደራጁ የፍተሻ ላቦራቶሪዎቹ አማካኝነት የምርትና የአገልግሎት ጥራት የማረጋገጥ፣ የምርትና የስራ አመራር ሰርተፊኬሽን እንዲሁም የኢንስፔክሽን አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል ብለዋል።

በዚህም ድርጅቱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመቱ ከ36 ሺህ በላይ የምርት ጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶችን መስጠቱን አስታውቀዋል።


በበጀት ዓመቱ የተሰጠው የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ5 ሺህ 500 በላይ አገልግሎቶች እድገት ያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል።

የድርጅቱን ተደራሽነት ለማስፋትና አገልግሎቱን ወደ ክልሎች ተደራሽ ለማድረግ በተሰራው ሰፊ ስራ በድሬዳዋ ከተማ የመጀመሪያ የሆነውን የነዳጅ፣ የምግብና የንጽህና መጠበቂያ ግብዓቶች ፍተሻ ላቦራቶሪ ስራ ማስጀመሩንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም በአዳማ ቅርንጫፍ ባለ አምስት ወለል ህንጻ በማስገንባት በምግብ፣ መጠጥና በግብርና ግብዓቶች ላይ ተጨማሪ የፍተሻ አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን በደሴና ኮምቦልቻ ያሉ ቅርንጫፎችንም የማዘመን ስራዎች መከናወናቸውን አብራርተዋል።

በምርትና ስራ አመራር ሰርተፊኬሽን ዘርፍ ከ900 በላይ ድርጅቶች የምርት ጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል።

ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶች ጥራታቸውን ጠብቀው እንዲገቡ በጅቡቲ ወደብ የጅምላ ጭነት ኢንስፔክሽን አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።

መንግስት የምርትና የአገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅ የጀመረው ሰፊ የሪፎርም ስራ ለተቋሙ ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን አስታውቀዋል።


ይህ የተከናወነው የሪፎርም ስራ ኢትዮጵያ ከተቀላቀለችው የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና እና ለመቀላቀል በድርድር ላይ ካለችበት የዓለም ንግድ ድርጅት አንጻር የሀገሪቱን የንግድ ልውውጥና ኢኮኖሚ ለማሳደግ መሆኑን አስረድተዋል።

ይህም ጥራታቸውን ያልጠበቁ የውጭ ምርቶች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ለመከላከልና የሀገር ውስጥ ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ትልቅ ሚና እንዳለው አብራርተዋል።

በዚህም በአፍሪካ ቀዳሚና ተወዳዳሪ የሆነ የጥራት ማረጋገጫ ተቋም መገንባቱን ዋና ዳይሬክተሯ ጨምረው ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026