የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በምዕራብ ወለጋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ470 በላይ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት በቅተዋል

Jul 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጊምቢ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ከ470 በላይ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃታቸውን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፋ ገለጹ።

ዋና አስተዳዳሪው እንደተናገሩት፤ ለአገልግሎት የበቁት እነዚህ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች የተገነቡት ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ነው።

በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተጠናቀው ወደ ሥራ ከገቡት የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች መካከል የንጹሕ መጠጥ ውኃ ተቋማት፣ የአነስተኛና ጥቃቅን ማኑፋክቸሪንግ ሼዶች፣ የመስኖ ልማት መሠረተ ልማቶች፣ የገጠርና የከተማ መንገዶች እንዲሁም የጤና ኬላዎች እና የትምህርት ተቋማት ናቸው ብለዋል።


የእነዚህ ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ መግባት በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም ከማጽናት ባለፈ፣ ሕዝቡ ልማቱን በማፋጠን የራሱን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴዎች በንቃት እንዲያሳልጥ ትልቅ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።

የዞኑ ነዋሪዎች በበኩላቸው ፤ በአካባቢው የተገነቡት ፕሮጀክቶች የሕዝቡን የቆየ የመልማት ፍላጎት በትክክል የመለሱ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዞኑ የተገነቡት የትምህርትና ጤና ተቋማት በቅርበት አገልግሎት እንድናገኝ እያስቻሉን ነው፤ ይህም ገንዘብና ጉልበታችንን በመቆጠብ በሌሎች የልማት ሥራዎች ላይ እንድንተጋ አግዞናል ብለዋል።


እንዲሁም በአካባቢያችን የተገነቡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች ምርታችንን በቀላሉ ወደ ገበያ በማድረስ ተጠቃሚ እንድንሆን እያገዘን ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

በቀጣይም የአካባቢያችንን ሰላምና ልማት ዘላቂ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከምንጊዜውም በላይ የበኩላችንን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁ ነን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026