🔇Unmute
ጊምቢ፤ ሐምሌ 1/ 2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ከ470 በላይ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃታቸውን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፋ ገለጹ።
ዋና አስተዳዳሪው እንደተናገሩት፤ ለአገልግሎት የበቁት እነዚህ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች የተገነቡት ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ነው።
በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተጠናቀው ወደ ሥራ ከገቡት የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች መካከል የንጹሕ መጠጥ ውኃ ተቋማት፣ የአነስተኛና ጥቃቅን ማኑፋክቸሪንግ ሼዶች፣ የመስኖ ልማት መሠረተ ልማቶች፣ የገጠርና የከተማ መንገዶች እንዲሁም የጤና ኬላዎች እና የትምህርት ተቋማት ናቸው ብለዋል።

የእነዚህ ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ መግባት በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም ከማጽናት ባለፈ፣ ሕዝቡ ልማቱን በማፋጠን የራሱን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እንቅስቃሴዎች በንቃት እንዲያሳልጥ ትልቅ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።
የዞኑ ነዋሪዎች በበኩላቸው ፤ በአካባቢው የተገነቡት ፕሮጀክቶች የሕዝቡን የቆየ የመልማት ፍላጎት በትክክል የመለሱ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በዞኑ የተገነቡት የትምህርትና ጤና ተቋማት በቅርበት አገልግሎት እንድናገኝ እያስቻሉን ነው፤ ይህም ገንዘብና ጉልበታችንን በመቆጠብ በሌሎች የልማት ሥራዎች ላይ እንድንተጋ አግዞናል ብለዋል።

እንዲሁም በአካባቢያችን የተገነቡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች ምርታችንን በቀላሉ ወደ ገበያ በማድረስ ተጠቃሚ እንድንሆን እያገዘን ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡
በቀጣይም የአካባቢያችንን ሰላምና ልማት ዘላቂ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከምንጊዜውም በላይ የበኩላችንን ድርሻ ለመወጣት ዝግጁ ነን ብለዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026