🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የምግብ ዋስትና የሚያረጋግጥ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ትግበራን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኅን በሰጡት መግለጫ፤ መርሃ ግብሩ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የኢኮኖሚ አቅም እየፈጠረ ነው።
መርሃ ግብሩ የአርሶና አርብቶ አደሩን የምግብና ሥርዓተ-ምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባሻገር፣ የከተሞችን የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች የገበያ ፍላጎት በማሟላት ጉልህ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ያለው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋጋ ንረትን በመቆጣጠር ረገድም ከፍተኛ ጠቀሜታ እያስገኘ መሆኑን አስረድተዋል።
የእንስሳት ሀብት ምርታማነትን በማሻሻል በኩልም፤ የወተት ላም ዝርያ ማሻሻልን ጨምሮ በዶሮና እንቁላል ምርት ዘርፍ ለወጣቶችና ለሴቶች በርካታ የሥራ ዕድሎችን መፍጠሩን አንስተዋል።
ለአብነትም የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከመጀመሩ በፊት በዓመት ይሰራጭ የነበረው 26 ሚሊየን የዶሮ ጫጩት ብቻ የነበረ ቢሆንም ዘንድሮ ግን ወደ 184 ሚሊዮን ማደጉን አስታውቀዋል።
ለውጭ ገበያ የሚቀርብ የስጋ ምርትን ለማሳደግ የተከናወኑ ዘመናዊ የከብት ማደለብ ስራዎችና የእንስሳት ክትባት ተደራሽነት መሻሻሎች፣የዘርፉን የኤክስፖርት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ እንዳሳደጉት አብራርተዋል።
ከዚህ ባሻገርም የኩሬ ዓሣ እርባታን በማስፋፋትና በዘመናዊ የንብ ማነብ ሥርዓት የዜጎችን የአመጋገብ ሥርዓትና የምርታማነት ባህል በማሳደግ የውጭ ምንዛሬን የሚያስገኝ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026