የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የምግብ ዋስትና የሚያረጋግጥ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው

Jul 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የምግብ ዋስትና የሚያረጋግጥ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ትግበራን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኅን በሰጡት መግለጫ፤ መርሃ ግብሩ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የኢኮኖሚ አቅም እየፈጠረ ነው።

መርሃ ግብሩ የአርሶና አርብቶ አደሩን የምግብና ሥርዓተ-ምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባሻገር፣ የከተሞችን የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች የገበያ ፍላጎት በማሟላት ጉልህ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ያለው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋጋ ንረትን በመቆጣጠር ረገድም ከፍተኛ ጠቀሜታ እያስገኘ መሆኑን አስረድተዋል።

የእንስሳት ሀብት ምርታማነትን በማሻሻል በኩልም፤ የወተት ላም ዝርያ ማሻሻልን ጨምሮ በዶሮና እንቁላል ምርት ዘርፍ ለወጣቶችና ለሴቶች በርካታ የሥራ ዕድሎችን መፍጠሩን አንስተዋል።

ለአብነትም የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከመጀመሩ በፊት በዓመት ይሰራጭ የነበረው 26 ሚሊየን የዶሮ ጫጩት ብቻ የነበረ ቢሆንም ዘንድሮ ግን ወደ 184 ሚሊዮን ማደጉን አስታውቀዋል።

ለውጭ ገበያ የሚቀርብ የስጋ ምርትን ለማሳደግ የተከናወኑ ዘመናዊ የከብት ማደለብ ስራዎችና የእንስሳት ክትባት ተደራሽነት መሻሻሎች፣የዘርፉን የኤክስፖርት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ እንዳሳደጉት አብራርተዋል።

ከዚህ ባሻገርም የኩሬ ዓሣ እርባታን በማስፋፋትና በዘመናዊ የንብ ማነብ ሥርዓት የዜጎችን የአመጋገብ ሥርዓትና የምርታማነት ባህል በማሳደግ የውጭ ምንዛሬን የሚያስገኝ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026

በክልሉ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግባር ይጠናከራል-ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 17/2018 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ተደራሽ የማድረግ ተግ...

Jun 25, 2026