የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የምግብ ዋስትና የሚያረጋግጥ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው

Jul 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የምግብ ዋስትና የሚያረጋግጥ ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ትግበራን አስመልክተው ለመገናኛ ብዙኅን በሰጡት መግለጫ፤ መርሃ ግብሩ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የኢኮኖሚ አቅም እየፈጠረ ነው።

መርሃ ግብሩ የአርሶና አርብቶ አደሩን የምግብና ሥርዓተ-ምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባሻገር፣ የከተሞችን የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች የገበያ ፍላጎት በማሟላት ጉልህ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጠ ያለው የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የምግብ ዋጋ ንረትን በመቆጣጠር ረገድም ከፍተኛ ጠቀሜታ እያስገኘ መሆኑን አስረድተዋል።

የእንስሳት ሀብት ምርታማነትን በማሻሻል በኩልም፤ የወተት ላም ዝርያ ማሻሻልን ጨምሮ በዶሮና እንቁላል ምርት ዘርፍ ለወጣቶችና ለሴቶች በርካታ የሥራ ዕድሎችን መፍጠሩን አንስተዋል።

ለአብነትም የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከመጀመሩ በፊት በዓመት ይሰራጭ የነበረው 26 ሚሊየን የዶሮ ጫጩት ብቻ የነበረ ቢሆንም ዘንድሮ ግን ወደ 184 ሚሊዮን ማደጉን አስታውቀዋል።

ለውጭ ገበያ የሚቀርብ የስጋ ምርትን ለማሳደግ የተከናወኑ ዘመናዊ የከብት ማደለብ ስራዎችና የእንስሳት ክትባት ተደራሽነት መሻሻሎች፣የዘርፉን የኤክስፖርት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ እንዳሳደጉት አብራርተዋል።

ከዚህ ባሻገርም የኩሬ ዓሣ እርባታን በማስፋፋትና በዘመናዊ የንብ ማነብ ሥርዓት የዜጎችን የአመጋገብ ሥርዓትና የምርታማነት ባህል በማሳደግ የውጭ ምንዛሬን የሚያስገኝ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026