🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2 /2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ቀጣናውን በኃይል የማስተሳሰር ሚናዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) ገለጹ።
የ22ኛው የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር አስቸኳይ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
ስብሰባውን አስመልክቶ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) ለመገናኛ ብዙኃን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ታንዛኒያ እና ሱዳን የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ሚናዋን እየተወጣች ነው።
በምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር ማዕቀፍም ሀገሪቱ ቀጣናውን በኃይል የማስተሳሰር ተግባሯን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል።
ይህ የኃይል ትስስር በቀጣናው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖርና ትስስሩን ይበልጥ ለማሳለጥ አስቻይ መድረክ መሆኑንም አንስተዋል።
የኃይል አቅርቦትን በማሳለጥ የተረጋጋ የሕዝቦችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ ዋነኛው ግባችን ነው ብለዋል።
ለሁለት ቀናት እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ የምክር ቤት ስብሰባ በአባል ሀገራቱ መካከል በጋራ ለመሥራት የተደረጉ ስምምነቶች እና የኤሌክትሪክ አገልግሎት ውሎችን ጨምሮ በተለያዩ አሠራሮች ላይ ውይይት ተደርጎ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል።
በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ገበያ ማዕከል የት ይሁን የሚለው ጉዳይ ሌላው ዋና የውይይት አጀንዳ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ገልጸዋል።
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...
Aug 21, 2026