🔇Unmute
ሚዛን አማን፤ ሐምሌ 3/2018(ኢዜአ)፦ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 348 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ መቅረቡን የክልሉ ማዕድን እና ኢነርጂ ኤጀንሲ አስታወቀ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰሞኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በወርቅ ምርት እመርታዊ ውጤት መመዝገቡን መግለጻቸው ይታወሳል።
በዚህም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከወርቅ ማዕድን ምርት 5 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማገኘት የሚያስችል አቅም መፈጠሩን ጠቅሰው፣ ኢትዮጵያ በብዝሀ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ለማዕድን ዘርፍ የሰጠችው ትኩረት ውጤቱን ከፍ ማድረጉንም ተናግረዋል።
የወርቅ ማዕድን ከሚመረትባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች አንዱ በሆነው ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልልም ለዘርፉ በተሰጠ ትኩረት የወቅር ምርት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መጥቷል።

ኢዜአ ያነጋገራቸው የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው ወልያብ (ዶ/ር) እንዳሉት፣ በክልሉ በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው የወርቅ አቅርቦት ምጣኔ ከፍተኛ ነው።
ለእዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 350 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ለማቅረብ ታቅዶ 348 ኪሎ ግራም ምርት መቅረቡን በማሳያነት ተናግረዋል።
አፈጻጸሙ በ2017 በጀት ዓመት ከክልሉ ከቀረበው 155 ነጥብ 5 ኪሎ ግራም የወርቅ ምርት አንጻር ሲታይ በከፍተኛ መጠን ጭማሪ ማሳየቱንም ገልጸዋል።
የለውጡ መንግስት ለማዕድን ዘርፍ በሰጠው ትኩረትና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ባደረጉት ጠንካራ ክተትል የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉንም ጠቁመዋል።
በ2019 በጀት ዓመትም ከዘንድሮ ከፍ ያለ የወርቅ መጠን ለብሔራዊ ባንክ በማቅረብ ሀገራዊ የውጭ ምንዛሬ አቅምን በማጠናከር በኩል ክልሉ ያለውን ሚና እንዲያሳድግ ቅንጅታዊ አሰራር ይጠናከራል ብለዋል።
ለዚህም ተደራጅተው ፈቃድ ያገኙ ወርቅ አምራች ማኅበራት በመሉ አቅም ወደ ተግባር እንዲገቡ በማድረግና አዳዲስ ማኅበራትን በማሰማራት የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማስቀጠል ይሰራል ነው ያሉት።
መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...
Jul 11, 2026
ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...
Jul 4, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...
Jul 3, 2026
አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...
Jun 29, 2026