የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ በመንግሥትና በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅት ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Jul 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ ሐምሌ 4/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በመንግሥትና በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅት በተሠራው ሥራ ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ።

ክልል አቀፍ የመንግሥትና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የጋራ ምክክር ፎረም በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ተፈሪ አባተ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የክልሉን ሀብት በአግባቡ በማስተዳደር፣ የዜጎችን የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሁም መሠረታዊ የኢኮኖሚ ለውጥ ለማምጣት በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

መንግሥት ለቀረጻቸው ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ስኬት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ልማት ግንባታ ውስጥ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።

ለዚህም ድርጅቶቹ በተለይ በውኃ፣ በሳኒቴሽንና ሃይጂን፤ በጤና እና በግብርና፣ በኑሮ ማሻሻያ እና በትምህርት እንዲሁም በአካባቢ ጥበቃ እንዲሁም በሌሎች ማኅበራዊ ዘርፎች ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

በቀጣይም መሠረታዊ አገልግሎቶችን ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ቅንጅታዊ አሠራሮች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።


የቢሮው ምክትልና የፊሲካል ፖሊሲ ትብብር ዘርፍ ኃላፊ ታምራት ታንጋ በበኩላቸው፤ የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማ በመንግሥትና በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች መካከል ያለውን አጋርነትና ትብብር ለማጠናከር ነው ብለዋል።

የሁለቱ አካላት ጥምረት የሕዝቡን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት የሚያሳድግ በመሆኑ በመካከላቸው ያለው ጥብቅ ትብብር ለክልሉ ዕድገትና ልማት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።


የክልሉ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ማስተባበሪያ ዋና ዳይሬክተር ማሞ ሙልሶ፣ የክልሉን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 11, 2026

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026