የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ በመንግሥትና በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅት ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Jul 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ ሐምሌ 4/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በመንግሥትና በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅት በተሠራው ሥራ ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ።

ክልል አቀፍ የመንግሥትና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የጋራ ምክክር ፎረም በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ተፈሪ አባተ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ የክልሉን ሀብት በአግባቡ በማስተዳደር፣ የዜጎችን የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሁም መሠረታዊ የኢኮኖሚ ለውጥ ለማምጣት በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

መንግሥት ለቀረጻቸው ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ስኬት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ልማት ግንባታ ውስጥ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።

ለዚህም ድርጅቶቹ በተለይ በውኃ፣ በሳኒቴሽንና ሃይጂን፤ በጤና እና በግብርና፣ በኑሮ ማሻሻያ እና በትምህርት እንዲሁም በአካባቢ ጥበቃ እንዲሁም በሌሎች ማኅበራዊ ዘርፎች ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

በቀጣይም መሠረታዊ አገልግሎቶችን ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ቅንጅታዊ አሠራሮች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።


የቢሮው ምክትልና የፊሲካል ፖሊሲ ትብብር ዘርፍ ኃላፊ ታምራት ታንጋ በበኩላቸው፤ የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማ በመንግሥትና በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች መካከል ያለውን አጋርነትና ትብብር ለማጠናከር ነው ብለዋል።

የሁለቱ አካላት ጥምረት የሕዝቡን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነት የሚያሳድግ በመሆኑ በመካከላቸው ያለው ጥብቅ ትብብር ለክልሉ ዕድገትና ልማት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።


የክልሉ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ማስተባበሪያ ዋና ዳይሬክተር ማሞ ሙልሶ፣ የክልሉን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሰው ሃይል ልማትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በጋራ ይሰራሉ - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴርኪን

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 14/2018 (ኢዜአ) ፦ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር በምርምር፣ በሰው ሃይል ልማት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር...

Aug 21, 2026