የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአዲስ አበባ በአምስት ዓመታት ውስጥ ከ1 ነጥብ 3 ትሪሊዮን ብር በላይ የካፒታል ኢንቨስትመንት መሳብ ተችሏል

Jul 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ሐምሌ 5 /2018 (ኢዜአ)፦በአዲስ አበባ በአምስት ዓመታት ውስጥ ከ1 ነጥብ 3 ትሪሊዮን ብር በላይ የካፒታል ኢንቨስትመንት መሳብ መቻሉን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን በዓድዋ ድል መታሰቢያ የምክር ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ እያካሄደ ይገኛል።


ከንቲባ አዳነች አቤቤ በጉባኤው ላይ የከተማ አስተዳደሩን የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት እያቀረቡ ነው።

ከንቲባዋ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ባቀረቡት የሪፖርት ማብራሪያ፤ ባለፉት አምስት ዓመታት የአዲስ አበባን የኢንቨስትመንት አማራጮች በማስተዋወቅና በማስፋፋት ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

በዚህም ለ22,190 አልሚ ባለሀብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ በመስጠት፣ ለ1,632 ነባር ባለሀብቶች ደግሞ የማስፋፊያ ፈቃድ መስጠት መቻሉን አስታውቀዋል።

የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከተሰጣቸው ውስጥ ከ2 ሺህ በላይ የሚሆኑት ወደ ሥራ በመግባት ከ54 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል በከተማዋ ኢኮኖሚ ውስጥ በማንቀሳቀስ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸዋል።

በመንግሥትና በግል አጋርነት በተቀረጹ የተለያዩ የልማት ዘርፎችና ፕሮጀክቶችም፣ በአምስት ዓመታት ውስጥ ከ1.3 ትሪሊዮን ብር በላይ የካፒታል ኢንቨስትመንት በመሳብ እመርታዊ ውጤት መገኘቱን አስታውቀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ የሀብት ፍሰትና የልማት መነቃቃት እያስተናገደች መሆኗን የጠቆሙት ከንቲባዋ፤ የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ በከፍተኛ ደረጃና ፍጥነት በማሳደግ፣ በርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሩዝ ልማት ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ አድርጓል

መቱ ፤ ሐምሌ 2/ 2018(ኢዜአ):- የሩዝ ልማት ስራ ላይ መሳተፋችን ምርታማነትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታችንን ለማሳደግ አስችሎናል ሲሉ በኢሉባቦር ዞ...

Jul 11, 2026

በክልሉ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም ለመጠቀም የተደረጉ ጥረቶች ውጤት አስመዝገበዋል

ሆሳዕና፤ ሰኔ 25/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማ...

Jul 4, 2026

የኦንላይን አገልግሎት መጀመሩ የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባለንበት ሆነን እንድናገኝ አስችሎናል 

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 24/ 2018 (ኢዜአ):- ኤጀንሲው ያስጀመረው የኦንላይን አገልግሎት የሲቪልና የነዋሪነት አገልግሎትን ባሉበት ሆነው በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻ...

Jul 3, 2026

በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የተጠናከረ የሰብል ጥበቃ ሥራ በቅንጅት እየተከናወነ ይገኛል

አዳማ ፤ ሰኔ 21/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተቀናጀ የሰብል ጥበቃ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ግብርና ...

Jun 29, 2026