የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በቡና የወጭ ንግድ የተመዘገበውን አበረታች ስኬት በቅመማ ቅመም መድገም የሚያስችል የምርታማነት አቅም እየተፈጠረ ነው

Sep 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 8/2019 (ኢዜአ):-በቡና የወጭ ንግድ የተመዘገበውን አበረታች ስኬት በቅመማ ቅመም ዘርፍም መድገም የሚያስችል የምርታማነት አቅም እየተፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን አስታወቀ።

የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የቅመማ ቅመም ዘርፉን ስልታዊ በሆነ መንገድ ለማዘመን አጠቃላይ ጥረቶች መጀመራቸውን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት ሮዝመሪ፣ ኮረሪማ፣ ጥቁር አዝሙድ እና ዝንጅብልን ጨምሮ 16 የተለያዩ የቅመማ ቅመም ዓይነቶች ለውጭ ገበያ እየቀረቡ ይገኛሉ።

ባለፈው የበጀት ዓመት ብቻ ከዚህ ዘርፍ 17 ሚሊዮን ዶላር ገቢ የተገኘ ሲሆን፣ አሁን ላይ ይህንን አፈጻጸም ወደ 20 ሚሊዮን ዶላር ለማሳደግ ታቅዶ እየተሠራ ነው።

ለእነዚህ 16 የቅመማ ቅመም ዓይነቶች የሚሆን ዘመናዊ የአመራረት፣ የጥራት አጠባበቅ እና የገበያ ሥርዓት ፓኬጆች ተዘጋጅተዋልም ብለዋል።

እነዚህን አዳዲስ ፓኬጆች ወደ መሬት ለማውረድ የሚያስችሉ ዝርዝር መመሪያዎችም መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

ተግባራዊነቱን ውጤታማ ለማድረግም በአርሶ አደሮች እና በግብርና ባለሙያዎች ላይ ያተኮረ ሥልጠና መሰጠቱን ጠቅሰዋል።

በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቀጠል የምርት ጥራት ወሳኝ በመሆኑ ጥብቅ የቁጥጥር ሥርዓቶች እየተዘረጋ ይገኛል ብለዋል።

በዚህ ረገድም ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር በምርት ጥራት ቁጥጥር ዙሪያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የትብብር ስምምነት መፈረሙን አስታውቀዋል።

አሁን ላይ በዓመት የሚመረተው የቅመማ ቅመም መጠን 10 ሺህ ቶን የደረሰ ሲሆን፣ ይህንን ወደ 13 ሺህ ቶን ከፍ ለማድረግና መዳረሻ ገበያዎችን ለማስፋት ግብ ተይዞ እየተሠራ ነው ብለዋል።

በድህረ ምርት ዙሪያ ለአርሶ አደሮች በፓኬጅ የተደገፉ ሥልጠናዎች ተደራሽ እየተደረጉ መሆኑ የምርት ጥራትን ለማረጋገጥ ዓይነተኛ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል።

እነዚህ የተቀናጁ ጥረቶች የኢትዮጵያን የቅመማ ቅመም ምርቶች ተወዳዳሪነት በማሳደግ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ከፍ እንደሚያደርጉት ይጠበቃልም ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የእጣንና ሙጫ ደኖችን ለመንከባከብ የማህበረሰብ አቀፍ የደን ጥበቃ ሥራዎች እየተካሔደ ነው

ገንዳውኃ፣ መስከረም 9/2019 (ኢዜአ):- የእጣንና ሙጫ ደኖችን በመንከባከብ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ የማህበረሰብ አቀፍ የጥበቃ ሥራዎች እየተካሔደ መ...

Sep 20, 2026

በባህር ዳር ከተማ አስተማማኝ ሰላምና ተጨባጭ የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል

ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል...

Sep 15, 2026

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026