የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የእጣንና ሙጫ ደኖችን ለመንከባከብ የማህበረሰብ አቀፍ የደን ጥበቃ ሥራዎች እየተካሔደ ነው

Sep 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውኃ፣ መስከረም 9/2019 (ኢዜአ):- የእጣንና ሙጫ ደኖችን በመንከባከብ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ የማህበረሰብ አቀፍ የጥበቃ ሥራዎች እየተካሔደ መሆኑን የሰሜን ጎንደር ደንና አካባቢ ጥበቃ ተጠሪ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡

የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ መልካም ዋሲሁን እንደገለጹት፣ የደን ሀብቱን በመንከባከብ፣ ዘመናዊ የእጣንና ሙጫ አመራረት መንገድን በመከተልና የምርት ጥራትን በመጠበቅ ለገበያ እንዲቀርብ እየተደረገ ይገኛል።


በዋናነትም የእጣንና ሙጫ ደኖችን በመንከባከብና በማልማት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እንዲቻል የማህበረሰብ አቀፍ የደን ጥበቃ ሥራዎች ላይ በማተኮር እየተሠራ ነው ብለዋል።

በዚሁ መስክ ሥራ አጥ ወገኖችን በማደራጀት ሕገ-ወጥ የደን ጭፍጨፋንና የደን ውጤቶች ዝውውርን በማስቆም ከዘርፉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉንም ነው የተናገሩት።

አምራቾችም ዘመናዊ የምርት አሰባሰብና የአያያዝ ዘዴዎችን በመከተል ጥራት ያለው የእጣንና ሙጫ ምርት ለማቅረብ እንዲችሉ እገዛና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በተጠናቀቀው የበጀት ዓመትም ከሰባት ሺሕ ኩንታል በላይ የእጣን ምርት ለገበያ በማቅረብ ከ374 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።

ከተገኘው ገቢ ውስጥም 74 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር የሚሆነው መንግሥት ከሮያሊቲ ክፍያ ገቢ ያደረገው መሆኑን አስረድተዋል።

በዞኑ የሌንጫ አዲስ ሕይወት ሕብረት ሥራ ማኅበር ሊቀመንበር አቶ በየነ ውቤ እንደገለጹት፣ እጣንና ሙጫ በማምረት ሥራ ላይ በማኅበር በመደራጀት ባለፈው ዓመት ወደ ማምረት ሥራ መግባታቸውን ይገልጻሉ።


በተጠናቀቀው የበጀት ዓመትም ማኅበራቸው 362 ኩንታል የእጣንና ሙጫ አምርቶ ለገበያ በማቅረብ ከ21 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ገልጸዋል።

ሌላው በመተማ ወረዳ በመሸሃ ቀበሌ በእጣን ምርት የተሰማሩት አቶ አየነው ሲሳይ፣ በተጠናቀቀው የ2018 ዓ.ም. ከአንድ ሺሕ ኩንታል በላይ እጣን ለገበያ ማቅረባቸውን ተናግረዋል።

በተደጋጋሚ በሚሰጣቸው ሥልጠና አማካኝነት ደኑን ሳይጎዱ ጥራቱን የጠበቀ እጣን ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ እንደሚገኙም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የእጣንና ሙጫ ደኖችን ለመንከባከብ የማህበረሰብ አቀፍ የደን ጥበቃ ሥራዎች እየተካሔደ ነው

ገንዳውኃ፣ መስከረም 9/2019 (ኢዜአ):- የእጣንና ሙጫ ደኖችን በመንከባከብ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ የማህበረሰብ አቀፍ የጥበቃ ሥራዎች እየተካሔደ መ...

Sep 20, 2026

በባህር ዳር ከተማ አስተማማኝ ሰላምና ተጨባጭ የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል

ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል...

Sep 15, 2026

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026