🔇Unmute
ባህር ዳር፤ መስከረም 9/2019 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ተቋራጮች ፕሮጀክቶችን በጥራትና በፍጥነት በመጨረስ ሁለንተናዊ እድገቱን በማፋጠን የበኩላቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተጠቆመ።
የአማራ ክልል ኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን በባህር ዳር ከተማ እያካሄደ ነው።

በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ከተሞች ክላስተር አስተባባሪ አሕመዲን መሀመድ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ የመደመር መንግሥት ፕሮጀክቶችን ፈጥኖ በመጀመርና በጥራት በመጨረስ ጠንካራ እሴቶችን ገንብቷል።
በዚህም ከተለመደው አካሄድ በመውጣት በፈጠራ፣ በፍጥነት፣ በጥራትና በቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ አሰራርን ተግባራዊ ማድረጉን አስረድተዋል።
የኮንስትራክሽን ዘርፉ ከነበረበት የዘመናት ውድቀት በማንሰራራት የክልሉ የአምስት ዓመት ስትራቴጂና የ25 ዓመቱ የአሻጋሪና የእድገት ፍኖተ ካርታ ግብን ለማሳካት የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ መምጣቱን ተናግረዋል።
ፕሮጀክቶችን በፍጥነትና በጥራት በመጨረስ ለሀገር እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት ለማዋል በዘርፉ የተሰማሩ ተቋራጮች ትልቅ ሚና እንዳላቸው አረጋግጠዋል።
በፕሮጀክት አስተዳደር ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመሙላት ክልሉንም ሆነ ሀገርን በትክክለኛው የእድገት አቅጣጫ እንድትጓዝ መንግሥትና ተቋራጮች በጋራ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የኮንስትራክሽን ማህበር አባላቱ አቅም ካላቸው የሀገር ውስጥና የአለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር ትስስር በመፍጠር መንግሥትና ህዝብ የጣለባቸውን ሚና እንዲወጡም አስፈላጊው እገዛ እንደሚደረግ አስገንዝበዋል።
የአማራ ክልል የኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር ፕሬዚዳንት አቶ ሙሉቀን ቢተው በበኩለቸው ማሕበሩ ፍትሃዊ የስራ ውድድር እንዲሰፍን እና ህጋዊና ስርዓት ያለው ግብይት እንዲተገበርና የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።
ማህበሩ የስነ- ምግባር ችግሮችን በማረም ዘርፉ ለሀገሪቱ እድገት ያለውን ከፍተኛ ሚና እንዲወጣ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት መስራቱን እንደሚቀጥል ነው የገለጹት።
ገንዳውኃ፣ መስከረም 9/2019 (ኢዜአ):- የእጣንና ሙጫ ደኖችን በመንከባከብ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ የማህበረሰብ አቀፍ የጥበቃ ሥራዎች እየተካሔደ መ...
Sep 20, 2026
ባህር ዳር፤ መስከረም 4/2019 (ኢዜአ)፦ በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል...
Sep 15, 2026
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026